- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Abyssinia Law | Making Law Accessible! By
- Hits: 16194
በአለማችን በየዓመቱ አምስት ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ሲጋራ በማጨስ ምክንያት በሚከሰቱ የጤና ችግሮች እንደሚሞቱም በዘርፉ የተደረጉ የተለያዩ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡ በታዳጊ አገሮች ውስጥ ያለዕድሜ የሚከሰተውን ከፍተኛ የሞት መጠንና ህመምተኛነት በማባባስ ረገድ ትምባሆ ወይንም ሲጋራ ማጨስ ቁልፍ ሚና እንዳለው የሚያመላክቱት እነዚህ ጥናቶች፤ የሲጋራ አጫሾች ቁጥር በአደጉት አገራት እየቀነሰ መምጣቱንና በአንፃሩ ደግሞ በታዳጊ አገራት በከፍተኛ መጠን በመጨመር ላይ መሆኑን ይጠቁሟሉ፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 15038
ሰላም እንዴት ናችሁ ውድ የአቢሲኒያሎው ድኅረገጽ ተከታታዮች! ዛሬ ስለሰላማዊ ሰልፍ እና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የማድረግ መብትዎ አንዳንድ የሕግ ድንጋጌዎችን ልንነግራችሁ ወደድን፡፡ መሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን አስመልክቶ በሀገራችን የሚጠቀሱ የሕግ መሠረቶች የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 30 ድንጋጌዎች እና የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 3/1983) ናቸው፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 18909
ሰላም እንዴት ናችሁ! ዛሬ የሰበር ቅሬታ ወይም አቤቱታ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸው ጉዳዮች አጭር ነገር ልናስታውሳችሁ ወደድን፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ጉዳይ በስር ፍርድ ቤት መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በመሆኑም በሰበር ሊታረምልኝ ወይም ሊታይልኝ ይገባል የሚል አንድ አቤቱታ አቅራቢ ማሟላት የሚገባቸው ወይም ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው አቅረበናል፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Abyssinia Law | Making Law Accessible! By
- Hits: 14506
አይዞት አይደንግጡ! የገዙት ሞባይል ርካሽ በመሆኑ ብቻ ወንጀለኛ ይሆናሉ ማለታችን አይደለም፡፡ ነገር ግን ከመደበኛ የግብይት ሥርዓት ውጭ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከግለሰቦች በርካሽ ዋጋ የምንሸምታቸው የሞባይል ስልኮች ፍርድ ቤት አስቀርበው በእሥራት ሊያስቀጡን የሚችሉበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Abyssinia Law | Making Law Accessible! By
- Hits: 12560
‹‹መሽናት ክልክል ነው›› ‹‹መሽናት በሕግ ያስቀጣል›› ‹‹አጥር ሥር የሚሸና ውሻ ብቻ ነው›› …ወዘተ በሀገራችን ልዩ ልዩ ቦታዎች የሚገኙ የክልከላ ጥቅሶች ናቸው፡፡ በአብዛኛው የሀገራችን ከተሞች በመንገድ ዳር ሲሸኑ ማየት የተለመደ ድርጊት ከመሆኑ ባሻገር ነውርነቱ ቀርቷል፡፡ በውነቱ ለከተማችን ሽንት ሽንት ማለት ወንዶች ተጠያቂዎች ነን፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 14452
ማንኛውንም ቤት፣ ለንግድ ቢሆን ለመኖሪያ፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ የሚያከራዩ ከሆነ ይህንን የሕጉን አንቀጽ ከግምት ያስገቡ፡፡ በ2001 ዓ.ም የወጣው የጸረ ሽብር አዋጅ አዋጅ ቁጥር 652/2001 በአንቀጽ 15 ማንኛውም ቤት፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ ወይም ተመሳሳይ መገልገያ አከራይ (ልብ ይበሉ አከራይ) የሆነ ሰው የተከራዩን ማንነት በዝርዝርና በጽሑፍ የመያዝ እንዲሁም በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የማሳወቅ ግዴታ አለበት ብሎ ደንግጓል፡፡
More Articles …
Page 2 of 3