- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 30734
ልደትና ሞት ጋብቻና ፍቺ የሰው ልጅ ሕይወት የሚጀመርባቸውና የሚጠናቀቅባቸው እንዲሁም የሚያልፍባቸው የሕይወት ኩነቶች ናቸው፡፡ እንግዲህ ወሣኝ ኩነት በመባል የሚታወቁት የልደት፣ የጋብቻ፣ የፍቺ እና የሞት ክስተቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ክስተቶች ወሣኝ ኩነቶች የተባሉበት ዋናው ምክንያት በየአገሮች ሕገ-መንግሥትና በዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች የታወቁ የሰብዓዊ፣ የማኅበራዊና የፖለቲካ መብቶችን ተፈጻሚ ለማድረግና ለመጠበቅ ወሳኝ የሆኑ ሕጋዊ የግለሰብ ማንነት መረጃዎች ምንጭ በመሆናቸው ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ኩነቶቹ የአንድን አገር ሕዝብ ብዛትና ዕድገትን በትክክል ስለሚያሳዩ፣ ለኅብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባሕላዊ አገልግሎት አሰጣጥ ለሚዘጋጁ ዕቅዶች ዝግጅትና አፈጻጸም እስከ ዝቅተኛው አስተዳደር ክፍል አልፎም በግለሰቦች ደረጃ ተፈላጊና ወሳኝ መረጃዎች በመሆናቸው ወሳኝ ኩነት ተብለዋል፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Gulele Justice By
- Hits: 13076
ቃብድ የሚለው ቃል በተለምዶ ቀብድ ብለን የመንጠራው ነው፡፡ ሕጋችን ቃብድ ስለሚለው እኛም ቃብድ ብለነዋል፡፡ ያው እናንተ ቀብድ ብላችሁ ተረዱት፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 13393
ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኛ ከሆኑ መሠረታዊ ሕጋዊ መብትና ግዴታ አለበዎት፡፡ ከአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታ ተያይዘው ያሉ መብቶች አጅግ በርካታ ቢሆኑም ዋና ዋና የሚባሉትን ግዴታዎች ቢያወቁ ለርሶ ጠቃሚ ይሆናል በሚል እምነት የአሠሪና ሠራተኛ ግዴታዎች ጠቅለል ባለ መልኩ አቅርበነዋል፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 10605
ፖሊስ ካስቆምዎ
- ፖሊሱን ማናገር አይጠበቅቦትም፡፡ ሁሉጊዜም ቢሆን ያለመናገር ወይም ዝም የማለት መብት አለዎት፡፡ ያለመናገር ወይም ዝም የማለት መብት ማለት በተጠረጠሩበት ወንጀል ምንም ዓይነት መግለጫ ያለመስጠት መብት ማለት ሲሆን ስምና አድራሻዎትን ወይም ስለማንነትዎ መናገር ግን {tip የወንጀል ሕግ አንቀጽ 807 (ትዕዛዝን አለመፈፀም):: ማንም ስሙን ወይም ማንነቱን እንዲነግር፣ ሥራዎን/ሙያውን፣ መኖሪያ ሥፍራውን፣ አድራሻውን ወይም የግል ሁኔታውን የሚመለከት ማናቸውንም ሌላ ዝርዝር ጉዳይ እንዲገልጽ የሥራ ግዴታውን በሚያከናውን አንድ የመንግሥት ሠራተኛ በአግባቡ ሲጠየቅ ወይም ሲታዘዝ እንቢተኛ የሆነ እንደሆነ ከአንድ መቶ በር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ወር በማይበልጥ የማረፊያ ቤት እሥራት ይቀጣል፡፡}ግዴታዎ{/tip} መሆኑን ያስታውሱ፡፡