- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 19808
ሰላም እንዴት ናችሁ! ዛሬ የሰበር ቅሬታ ወይም አቤቱታ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸው ጉዳዮች አጭር ነገር ልናስታውሳችሁ ወደድን፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ጉዳይ በስር ፍርድ ቤት መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በመሆኑም በሰበር ሊታረምልኝ ወይም ሊታይልኝ ይገባል የሚል አንድ አቤቱታ አቅራቢ ማሟላት የሚገባቸው ወይም ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው አቅረበናል፡፡
Read more: የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ፋይል ለማስከፈት መሟላት ስለሚኖርባቸው ጉዳዮች
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Abyssinia Law | Making Law Accessible! By
- Hits: 15281
አይዞት አይደንግጡ! የገዙት ሞባይል ርካሽ በመሆኑ ብቻ ወንጀለኛ ይሆናሉ ማለታችን አይደለም፡፡ ነገር ግን ከመደበኛ የግብይት ሥርዓት ውጭ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከግለሰቦች በርካሽ ዋጋ የምንሸምታቸው የሞባይል ስልኮች ፍርድ ቤት አስቀርበው በእሥራት ሊያስቀጡን የሚችሉበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Abyssinia Law | Making Law Accessible! By
- Hits: 13259
‹‹መሽናት ክልክል ነው›› ‹‹መሽናት በሕግ ያስቀጣል›› ‹‹አጥር ሥር የሚሸና ውሻ ብቻ ነው›› …ወዘተ በሀገራችን ልዩ ልዩ ቦታዎች የሚገኙ የክልከላ ጥቅሶች ናቸው፡፡ በአብዛኛው የሀገራችን ከተሞች በመንገድ ዳር ሲሸኑ ማየት የተለመደ ድርጊት ከመሆኑ ባሻገር ነውርነቱ ቀርቷል፡፡ በውነቱ ለከተማችን ሽንት ሽንት ማለት ወንዶች ተጠያቂዎች ነን፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 15013
ማንኛውንም ቤት፣ ለንግድ ቢሆን ለመኖሪያ፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ የሚያከራዩ ከሆነ ይህንን የሕጉን አንቀጽ ከግምት ያስገቡ፡፡ በ2001 ዓ.ም የወጣው የጸረ ሽብር አዋጅ አዋጅ ቁጥር 652/2001 በአንቀጽ 15 ማንኛውም ቤት፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ ወይም ተመሳሳይ መገልገያ አከራይ (ልብ ይበሉ አከራይ) የሆነ ሰው የተከራዩን ማንነት በዝርዝርና በጽሑፍ የመያዝ እንዲሁም በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የማሳወቅ ግዴታ አለበት ብሎ ደንግጓል፡፡
Read more: ያከራዩትን ሰው ማንነት አለማሳወቅ ከ3 እስከ 10 ዓመት ጽኑ እሥራት እንደሚያስቀጣ ያውቃሉ?
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 12180
ሰላም የአቢሲኒያ ሎው አንባብያን አንዴት ከርማችኋል፡፡ መብትና ግዴታዎን ይወቁ በሚል ርዕስ ዘርፈ ብዙ ሀሳቦችን እያነሳን መብትና ግዴታችንን የማስተዋወቅ አምድ ከከፈትን ቆየት አልን፡፡ ይህ መብትና ግዴታዎትን ይወቁ በሚል ርዕስ የጀመርነውን ሃሳብ በጣም ጠቃሚ ነው ቀጥሉበት ላላችሁን ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡
- Details
- Category: Know Your Legal Rights - መብትና ግዴታዎን ይወቁ
- Liku Worku By
- Hits: 23259
የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች አቀራረብ
የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ - ሙስና ኮሚሽን የሙስና ወንጀልና ብልሹ አሰራርን በተመለከተ ጥቆማዎች የሚቀርቡባቸውን መንገዶች በግልጽ አስቀምጧል፡፡ በዚህ መሠረት ሙስና ወይም ብልሹ አሠራር ተፈጽሟል ብለው የሚያምኑ ከሆነ ከዚህ በሚከተለው መልኩ ማስታወቅ ይቻላል፡፡