የሕዝብ ተሳትፎ በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ያለው ሚና

ቀደም ባሉት ጊዜያት የፍትሕ ሥርዓት ቅቡልነት እና የሕዝብ አመኔታ መሠረት ተደርገው የሚወሰዱት ቢሮክራሲ፣ ምክንያታዊነት እና ሞያን መሠረት ማድረግ ነበር፡፡ በመሆኑም በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ዋና ተዋናዮች የሕግ ባለሞያዎች እና ሌሎች የፍትሕ አካላት ባለሞያዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ማህበረሰብ አካላትን ያገለለ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ስለሆነም መንግሥት እና የሕግ ሰዎች ፍትሕ የማስፈን ሀላፊነትን በብቸኝነት በመያዝ አባታዊ የአስተዳደር ዘዴ (Paternalistic Approach) ሲከተሉ ነበር፡፡ የዚህም አጠቃላይ አሠራር ሁሉን ነገር ለባለሙያ የመተው (Leave to the professional) የምንለው ነው፡፡ ይህም የወንጀል ተጠቂዎችን እና ባለጉዳዮችን እንዲረሱ በማድረግ ኒልስ ክሪስቲ እንደተባሉ አንድ ፀሐፊ አባባል “የራሳቸውን ጉዳይ በባለሙያዎች ተሰርቀዋል”፡፡

  12185 Hits