ማስታዎሻ፡- ውደ አንባቢያን ይህ ጽሑፍ የተወሰደው በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያዎች በሚል ከታተመው በ2017 ዓ.ም ተሻሻሎ በቀረበው መጽሐፌ ላይ ሲሆን የግርጌ ማስታዎሻዎቹ እና ማጣቀሻዎቹ ለዚህ ጽሑፍ ሲባል ለንባብ በሚመች አግባብ እንደገና ተቀናጅተው ተሰርተዋል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የተካተቱት አብዛኛዎቹ ነጥቦች አወዛጋቢ ሆኖም በሕግ ባለሙያው ብዥታ እና ልዩነት የሚፈጥሩ ነጥቦች በመጽሐፉ የመጀመሪያ ዕትም ያልነበሩ አሁን ላይ በችሎት በሚገጥሙ ክርክሮች ሰበር ጭምር መፍትሔ የሰጣቸውን እና ሰበር መፍትሔ ያልሰጠባቸውን ደግሞ የመጽሐፉ አዘጋጅም የራሱን ምልከታ እና መፍትሔ የሚላቸውን ሃሳቦች ያሰቀመጠባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡
“Law is nothing else, but the best reason of wise men applied for ages to the transaction and business of mankind” Abraham Lincoln
መነሻ ክስተት
ነገሩ እንዲህ ነው! የሙያ ባልደረቦቼ ደንበኞቻቸው ተከሳሽ በሆኑባቸው የፍትሐብሔር የፍርድ ሂደት ላይ መከላከያ መልሳቸውን ሲያቀርቡ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 244(2) (ለ) መሠረት “ክስ የቀረበበት ጉዳይ አስቀድሞ በፍርድ የተወሰነ” መሆኑን እና (ሠ) መሠረት የቀረበው ክስ “በይርጋ የታገደ” መሆኑን ጠቅሰው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያቸውን በዋናው ክርክር ላይ ካላቸው መልስ ጋር አያይዘው አቅረበው ነበር፡፡ ነገር ግን ፍ/ቤቶች በቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ ክርክር ለመስማት በተያዘ ቀነ ቀጠሮ ከሳሾች ሳይገኙ በመቅረታቸው ምክንያት ጉዳዩን እየመረመሩ የነበሩት ፍ/ቤቶች ተከሳሾች የቀረበባቸውን ክስ እንደሚክዱ ከጠየቁ በኃላ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 73 መሠረት ክስ ለመስማት በተያዘ ቀነ-ቀጠሮ ከሳሾች ባለመቅረባቸው እና ተከሳሾች ክደው በመከራከራቸው መዝገቡን ዘግተናል በማለት ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡
An interesting article, published on Jimma University Journal of Law, entitled “the immediate appealability of a court order against arbitration: it should be allowed and even made compulsory”, argues that an immediate appeal against a court order which is against arbitration must be allowed; article 320/3/ of the Civil Procedure Code should be amended to take the special nature of arbitration into account.