ቀለብ የመስጠጥ ግዴታ ፅንሰ ሀሳብ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

 

1. መግቢ

ግዴታ ህጋዊ ግንኙነት ሲሆን መሰረታዊ መርሁም የሚያካተው አንድ ዕዳ ያለበት ሰው ወይም ባለዕዳ ለአበዳሪው ዕዳውን የሚፈጽምበት ሂደት ነው፡፡ በዚህ ግንኙነት ውስጥ ባለዕዳው ለአበዳሪው አንድን ነገር ለማድረግ ፣ ለመስጠት ወይም ላለማድረግና ላለመስጠት የሚያደርገው ህጋዊ ግዴታ ነው፤ በተቃራኒው ደግሞ አበዳሪው ከባለዕዳው የሚገባውን እና በሕግ የተፈቀደለትን ጥቅም የሚያገኝበት ሁነት ነው፡፡ ግዴታዎች ከሁለት ምንጮች ይቀዳሉ፤ የመጀመሪያው ከውል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከሕግ ነው፡፡ ከውል የሚመነጭ የግዴታ አይነት በተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ላይ የሚመሰረት ሲሆን ስምምነቱም በተዋዋይ ወገኖቹ ላይ እንደ ሕግ እንደሚያገለግል የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 1731 ያትታል፡፡ ሁለተኛው የግዴታ ምንጭ ደግሞ ከሕግ የሚመዘዝ ነው፤ የዚህ አይነት ግዴታዎች በቀጥታ ከሕግ  የሚመነጩ ሲሆን ግዴታውም በባለዕዳው እና አበዳሪ ሰዎች ሊቀየር ፣ ሊሻሻል እንዲሁም ሊቀር አይችልም፡፡       

ቤተሰብ የአንድ ማህበረሰብ በጣም ጠቃሚ እና መሰረት የሆነ አካል ነው፡፡ ቤተሰብ አንድ ግለሰብን ከአጠቃላይ ማህበረሰብ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ ድልድይ ነው፡፡ እንዲሁም ተፈጥሮዊ ኢኮነሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ጥቅም አለው፡፡ ቀለብ የመስጠት ግዴታ በአብዛኛው በቤተሰብ መካከል የሚገኝ ሲሆን ተገላቢጦሽ ባህሪ አለው፡፡ ይህም ወላጆች ለልጆቻቸው ለሚያደርጉላቸው እንክብካቤ እና ለማሳደግ ላለባቸው ግዴታ ልጆችም በተራቸው ለቤተሰቦቻቸው በዕርጅና ወቅት፣ በችግር ላይ ላሉ ወንድም እና እህት እና ለሚወልዷቸው ልጆች ቀለብ የመስጠት ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ዋንኛ ምንጩ ከሕግ ቢሆንም በስምምነት ግዴታውን መመስረት ግን በግልጽ በሕግ አልተከለከለም፡፡ ይህ የሆነውም ቀለብ የመስጠት ግዴታ መሰረቱ በቤተሰብ መካከል የሚገኝን ግብረገባዊ ወይም ስነ-ምግባራዊ የመተጋገዝ ፣ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ተግባር ስለሆነ ነው፡፡    

 

Continue reading
  13527 Hits