የግልግል ዳኝነት የፍትሐ ብሔር ሕግ ሥራ ላይ ከዋለበት ከ1952 ዓ.ም ጀምሮ የሕግ ማዕቀፍ ያለዉ ቢሆንም ቀደም ሲል በነበሩ ጊዜያቶችም ባሕላዊ ደንቦችን መሰረት ባደረገ መልኩ ይፈፀም ነበር፡፡ የግልግል ዳኝነትን ጨምሮ አማራጭ የሙግት መፍቻዎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 3307 እስከ ፍ/ብ/ሕ/ቁ 3346 በተቀመጡ ደንቦች እንዲሁም በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 315- 319፣ 350- 357 በተቀመጡ ደንቦች የግልግል ዳኝነት ይመራ ነበር፡፡ እነዚህን የሕግ ማዕቀፎች መሰረት በማድረግ የግልግል ዳኝነት በአብዛኛዉ በሚባል ደረጃ ተቋማዊ ባልሆነ መልኩ ወይም ጊዜያዊ በሆነ የግልግል ዳኝነት /Ad hoc arbitration/ ቆይቷል፡፡ አሁን ላይ በሀገራችን ያለዉ የግልግል ዳኝነት በሁለት መልኩ ሊገለጽ የሚችል ነዉ፡፡ የመጀመሪያዉ ደግሞ ጊዜያዊ የግልግል ዳኝነት (Adhoc arbitration) ሲሆን ሁለተኛ ተቋማዊ የግልግል ዳኝነት (institutional arbitration) ነዉ፡፡
Arbitration has been a prevalent method of dispute settlement, in various countries of the world of today and yesterday. Arbitration is defined in the Black’s Law Dictionary as “a method of dispute resolution involving one or more neutral third party who the disputing parties usually agree to and whose decision is binding.”