The blogger has an LLB from the University of Gonder. He can be reached at kidist.elinor@yahoo.com

አንዳንድ ምልከታዎች ስለ መገናኛ ብዙኃን እና የሐሰት ዘገባዎች

ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እጅግ መሠረታዊ መብት ከመሆኑ የተነሳ የተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ ጥበቃ የሚያደርጉለት ሲሆን በአለማችን ላይ በአንባገነንነታቸው የሚታወቁ መንግሥታት ሰይቀሩ መብቱ ሳይሸራረፍ በሀገራቸው እንደሚጠበቅ ይከራከራሉ። በዚህ ጽሑፍ ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት በሰፊው ከሚተገበርበት ስለ መገናኛ ብዙኃን መብት እንመለከታለን። በመጀመሪያው ክፍል የመገናኛ ብዙኃን ለምን የሐሰት ዘገባዎችን ይሠራሉ በተለይም በመንግሥት ይዞታ ሥር የሚገኙ ወይም ዋነኛ የፋይናንስ ምንጫቸው በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ከመንግሥት የሆነ የሚለውን እናያለን። በመቀጠል የመገናኛ ብዙኃን የሰሩት ፕሮግራም እውነታን ያዘለ ሆኖ ሳለ የእርምት ወይም መልስ የመስጠት መብት ያለው አካል ሐሰተኛ ማስተባበያ ይዞ ቢቀርብ የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው ወይስ የለባቸውም የሚለውን እንመለከታለን። በመጨረሻም ነፃ ሚዲያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ከሀገራችን ሕጎች አንፃር አጭር ዳሰሳ እናካሔዳለን።

  9323 Hits
Tags: