About the Law - ስለሕጎቻችን

በዚህ ክፍል ስለሕጎቻችን እንጽፋለን፣ እንወያያለን እንዲሁም ጠቃሚ መፍትሔዎችን እንጠቁማለን፡፡ በተለይ አንድን ችግር ለመፍታት ወይም አንድን ድርጊት ለመቆጣጠር ከወጡ ሕጎች መካከል ሕጉ በሚፈልገው መጠን ያልተተገበሩ የሕግ ድንጋጌዎችን፣ ዝርዝራቸው በሕግ ይወሰናል ተብሎ ያልተወሰኑ ድንጋጌዎችን፣ መሻሻል የሚገባቸውን ሕጎችን እንዲሁም ሕግ ሊወጣላቸው የሚገቡ ርዕሰ ጉዳዮችን እንዳስሳለን፡፡ 

የህሊና ጉዳት ካሳ የተጎጂውን የስሜት መጎዳት ከግንዛቤ ባስገባ ሁኔታ መወሰን እንዳለበት ብዙዎቹ ይስማማሉ። የህሊና ጉዳት በተጎጂው ላይ የደረሰውን የስሜት መጎዳት፥ የስነ-ልቦና ጉዳት፥ ሐዘን፥ ሀፍረት፥ ውርደት ወዘተ... የመሳሰሉትን ጉዳቶች ያካትታል።

ይሁን እንጂ በፍታብሔር ሕጉ ካሳ የሚያስገኙ የህሊና ጉዳት ዓይነቶች እና ለህሊና ጉዳት የሚከፈለው የካሳ መጠን የጉዳት ካሳ መርህን በሚቃረን መልኩ የተጎጂውን ተገቢውን ካሳ የማግኘት መብት የሚያጣብብ ነው የሚል እምነት አለኝ። ለዚህም ምክንያት የማደርገው፦

የኮንዶሚኒየም ቤትን (የጋራ ህንፃን) አስመልክቶ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 370/1995 ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአስተዳደሩን ቤቶች የማስተላለፍ ኃላፊነትና አፈፃፀሙን ለመወሰን በወጣው አዲስ ነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር 19/97 አንቀፅ 14 (2) ላይ የኮንዶሚኒየም ቤት እጣ የደረሰው ሰው ዕጣው ከደረሰው ቀን አንስቶ እስከ አምስት ዓመት ድረስ ለሶስተኛ ወገን በሽያጭ ወይም በስጦታ ለማስተላለፍ የማይችል ስለመሆኑ ተመልክቷል፡፡ condoባለ እጣው እጣ ከደረሠው ቀን ጀምሮ አምስት ዓመታት ሳይሞላ ቤቱን አስመልክቶ በማናቸውም ሁኔታ የባለቤትነት መብቱን ለማስተላለፍ ውል እፈፅማለሁ ቢል የሠነዶች ማረጋገጫ ፅ/ቤት በዚህ ሕግ መሠረት አምስት ዓመት ሳይሞላ ማስተላለፍ እንደማይቻል በመግለፅ ተዋዋዮችን ይመልሳል፡፡

ባለንበት ዘመን ሕገ መንግሥት ወይም ስለመንግሥት አሠራርና አመራር የሚደነግግ ሕግ የሌሎው ሀገር ለማግኘት ያስቸግራል፡፡ ሳስበው ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት መደንገግና በዛው ልክ መቆጣጠር ያስፈለገበት መሠረታዊ ምክንያት የሰው ልጅ ካለፈባቸው የችግርና የጦርነት ውጤት የቀሰመው አብይ መፍትሔ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ አብዛኞቹ ሀገራት በሕገ መንግሥታቸው ውስጥ ከሚያካትቱት መሠረታዊና ጥቅል ድንጋጌዎች መካከል የመንግሥት ሥልጣንና ተግባር፣ የዜጎች መሠረታዊ መብትና ግዴታ፣ የመንግሥት አስተዳደርና የሥልጣን ክፍፍል እንዲሁም የአሠራር ሁኔታ ይገኙበታል፡፡

Page 2 of 2