በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ቤት የሰራ ሰው መብት - አንዳንድ ነጥቦች 

ሲፈጠር የአንድ ቤተሰብ የነበረው መሬት ቤተሰቡ በቢሊዮን ሲራባ አንድ ኢንች አልጨመረም። በመንኮራኩር ሰማይ ቢታሰስ በሮኬት ጠፈር ቢሰነጠቅ በምድር ላይ እንዳለው ያለ መሬት እስካሁን አልተገኘም። በምድር ያለው መሬትም በተለያዩ ምክንያቶች ጠቀሜታው እየቀነሰ፣ ለምነቱ እየጠፋና እየጠበበ ይገኛል። መሬት በገጠርም ሆነ በከተማ ዋነኛ የመብት ምንጭ እና የሁሉም ምጣኔ ሀብታዊ፣ ማሕበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች መሰረት ነው። እያለቀ የሄደውን መሬት እየጨመረ ላለው ሕዝብ በሚዛን ለማከፋፈል በተለያዩ ሀገራት በተለያዩ ጊዜያት ልዩ ልዩ ፍልስፍናዎች ሲፈለሰፉ፣ ርዕይዎተ ዓለም ሲሆኑ፣ ወደፖሊሲ ሲቀየሩና ሕግ እየሆኑ ሲተገበሩ ቆይተዋል። እየተተገበሩም ይገኛሉ። ይሁን እንጂ በዚህ ዘመን ለሁሉም ዜጎች መሬት መስጠት የሚያስችል ምንም ዓይነት ፍልስፍና አልተገኘም። 

  4340 Hits

Joint Ownership of Land and Right of Secession in the FDRE Constitution

Ethiopia is the home to more than 80 ethnic communities with different languages, cultural and religious diversity. Except in a few urban areas such as the capital city, most of Ethiopia's ethnic communities predominantly live in their respective distinct geographic areas of habitation. There is no ethnic community in Ethiopia a majority that comprises a population of more than 50% of the total population of Ethiopia.  But  there  are  relatively  significant  majority  ethnic  communities  such  as  the Oromo and Amhara. Most of Ethiopia's ethnic communities are divided along mainly two religious cleavage lines: Islam and Orthodox Christianity. By crosscutting Ethiopia's ethnic cleavage lines, religion plays a moderating role in limiting the intensity of the ethnic factor in politics, giving rise to overarching loyalty.

  17103 Hits

በገጠር መሬት የመጠቀም መብትን በዋስትና ማስያዝና አርሶ አደሩ

መሬት ካለው ተፈጥሮዋዊ ባሕርይም ሆነ ግዙፍነት የተነሳ በሃገራችን ፖለቲካል ኢኮኖሚ ማዕከል ሆኖ እስካሁን ዘልቋል፡፡ በተለይም አብዛኛው ሕዝብ በእርሻ  የሚተዳደር ባለበት ሃገር የመሬት ጉዳይ የኢኮኖሚያዊ መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ የሆነ ጠቀሜታ አለው፡፡ የሃገሪቱን የመሬት ስሪት (land tenure) ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከተው በእያንዳንዱ ሥርዓት የተለየ ባሕርይ ይዞ እናገኘዋለን፡፡

  31088 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ግብርና እድገትና የመሬት ፓሊሲና ሕግ

ግብርና የሃገራችን ወሳኝ የኤኮኖሚ ዘርፍ ነው። ምጣኔ ሃብት ምሁሮች እንደሚሉት፥ በቅጥርና አገራዊ ምርት የግብርናው ድርሻ እንዲቀንስ (በሌሎች ዘርፎች እንዲተካ)፥ ግብርናው በፍጥነት ማደግ አለበት። ለማነስ፤ በፍጥነት ማደግ። የግብርና እድገት ምን ይጠይቃል? የመስኖ መሰረተልማት። የተሻሻለ ግብአት፥ ምርጥ ዘር፥ ማዳበሪያ፥ አረም ማጥፊያ። የምርት ገበያ። መሬት። ጉልበት። እውቀት። የገጠር መንገድ። የአርብቶ እና አርሶ አደሮች ትምህርት። የገጠር የጤና አገልግሎት። የገጠር የመጠጥ ውሃ አገልግሎት። የገጠር ሃይል አቅርቦት። የገጠር ሰላምና ደህንነት ማስከበር። የግብርና ግብይቶችን እና ድርጅቶችን መጠበቅ።

  13236 Hits

ተጨማሪ ሃሳቦች ስለ ግብርና እድገትና የመሬት ፓሊሲና ሕግ

ከዚህ በፊት ባለው ጽሁፍ የሚከተሉትን ሃሳቦች አቅርቤ ነበር። በዋናነት የእነዚህ ሃሳቦች ተግባራዊነት ዉጤት፤ አሁን ተበጣጥሶ የሚገኘውን በገጠር መሬት ላይ የግብርና ውሳኔ መብት በአንጻራዊነት እንዲማከል ማድረጉ ነው። የግብርና ውሳኔ ማለት፥ በአንድ እርሻ ላይ ምን ላምርት? መቼ ላምርት? ምን አይነት እና መጠን ያለው ማዳበሪያ ልጠቀም? ምን አይነት የውሃ ቴኬኖሎጂ ልጠቀም? ምን አይነት ማረሻ፥ ማጨጃ፥ እና መውቂያ ልጠቀም? ምን አይነት የመሬትና አፈር ጥበቃና አስተዳደር አሰራሮችን ልከተል? እና የመሳሰሉት ናቸው። ከግብርና ውሳኔዎች ጋር የሚገናኙ የገበያ ውሳኔዎች ይኖራሉ። ለምሳሌ፤ ምን ያህል ምርቴን፥ መቼ፥ ለማን ልሽጥ? ምን ያህል ገንዘብ፥ ከማን፥ በምን ያህል ወለድ ልበደር? እነዚህና የመሳሰሉት ገበያ ነክ ውሳኔዎች ካነሳኋቸው ነጥቦች ጋር በቀጥታ አይገናኙም። እኔ ያነሳሁት የግብርና ውሳኔዎችን ነው።

  10929 Hits

የተሻሻለው የአማራ ክልል የገጠር መሬት አዋጅ እና አከራካሪው የይርጋ ድንጋጌ

የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 133/98 የተካው የተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 ቀደም ሲል በሕግ ደረጃ ሽፋን ያላገኙ አዲስ ነገሮችን ይዞ እንደወጣ ይታወቃል፡፡ አዲስ ከሚባሉ ነገሮች አንዱ በገጠር መሬት ላይ በሚነሱ ክርክሮች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚ ሊሆን እንደማይችል ያስቀመጠው ነገር ነው፡፡ ይህ የይርጋ ድንጋጌ በሕጉ የተካተተ አዲስ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ገና ከጅምሩ አከራካሪ ጉዳይ እየሆነ መጥቷል፡፡ አከራካሪነቱም በባለሙያዎች መካከል ሁለት ጫፍ የያዙ አቋም እንዲኖር ከማድረግ አልፎ አዲስ የክርክር ምክንያትም እየሆነ ነው፡፡ አዋጁ ስራ ላይ ከዋለ ጀምሮም የገጠር መሬትን ተከትሎ የሚቀርቡ ክሶች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚነት የለውም በሚል  ብዙ ዶሴዎች ከተዳፈኑበት አቧራቸውን እያራገፉ በክስ መልክ  እየቀረቡ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በባለሙያዎች መካከል በይርጋው ተፈፃሚነት ላይ  ባለ ሁለት ጫፍ የያዘ አቋም ምክንያት ከወዲሁ ተገማችነታቸውና ወጥነታቸው አደጋ ላይ እየወደቀ ነው፡፡ ስለዚህም በጉዳዩ ዙሪያ  የሚነሱ አቋሞችን እና ምክንያቶችን በማየት ሃሳቡን መመልከቱ አስፈላጊ እና ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ የፁሁፉ ዋና ትኩረትም በተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ላይ የተቀመጠጠው የይርጋ ድንጋጌ ወሰን አለው ወይስ የለውም የሚል ይሆናል፡፡

  48904 Hits

የግብይት ወጪ በግብርና

የግብይት እና የምርት ወጪ የሚባሉ ሁለት መሰረታዊ ወጪዎች አሉ። የምርት ወጪ የምትለው፥ አንድን አገልግሎት ወይም ሸቀጥ ወይም ነገር ለማምረት የምታወጣው ነው። ቋሚ እና ተቀያያሪ ወጪ ሊሆን ይችላል። ቋሚ የሚባለው ወጪ መጠን፥ በምርትህ መጠን አይወሰነም እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ። ስለዚህ አንድም አመረትህ ሺተሚሊዮን ቋሚ ወጪዉ ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ ብዙ ማምረት ከመጠን እንድትጠቀም ያደርግሃል። ነገር ግን ምን ታመርታለህ? ምንድን ነው ፍላጎትህ? ያመረትከውንስ ለማን እና በምን ያህል ትሸጣልህ? ግብይት ከማን ጋር ትፈጽማለህ? በድርድር ሂደት ያኛው ተዋዋይ ወገን የሚነግርህን መረጃ እንዴት ታረጋግጣለህ? ያኛው ሰውየ ያልነገረህ መረጃ ስለመኖሩ እንዴት ታረጋግጣለህ? እንዴት ትደዳደራለህ? ስምምነት ከገባህ በዃላ ያኛው ሰው ግዴታውን ለመወጣቱ ምን ማረጋገጫ አለህ? ግዴታውንስ በተባለው መጠን እና ጥራት ስለመወጣቱ እንዴት ትከታተላለህ? እነዚህ ሁሉ የግብይት ወጪ ይባላሉ።

  10312 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

  14061 Hits
Tags: