የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ፡፡
ዶ/ር አዲሱ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር በመሆን ያለፉትን ሁለት አጠቃላይ ምርጫዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ ገዢው ፓርቲና አጋሮቹ 547ቱንም የፓርላማ መቀመጫ ያሸነፉበትን የ2007 ዓ.ም አጠቃላይ ምርጫ በመምራት በሕግ የተፈቀደላቸውን የሥልጣን ዘመን አጠናቀዋል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የዶ/ር አዲሱን፣ የምክትል ኮሚሽነርና የኮሚሽን አባላት ሹመት በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል፡፡ በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ላለፉት አምስት ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና በዶ/ር አዲሱ ተተክተዋል፡፡