Federal Supreme Court Cassation Decisions

በኢትዮጵያ የታክስ አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የተርን ኦቨር ታክስን በመጠቀም ከሕግ አገልግሎት ላይ የሽያጭ ታክስ እንደ ሁኔታው በፌዴራሉና በክልል መንግስታት በመጣሉ በተግባርም እየተሰበሰበ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጅ ይህ ታክስ ሕጋዊ መሠረቱን እና አግባብነቱን በተመለከተ፤ ከታክስ መሠረቱ፣ ከታክስ ምጣኔው እና ከአስተዳደር ሂደቱ ጋር ተያይዞ በርካታ አዙሪት ጥያቄዎችና መውሰብስቦች ይስተዋላሉ፡፡ የዚህ ጥናት ዓላማም አነዚህን አዙሪት ጥየቄዎችና መውሰብስቦች በዓይነታዊ የምርምር ዘዴ በማጥናት የመፍትሔ ኃሳብ መጠቆም ነው፡፡ ለዚህም ያስችል ዘንድ የተለያዩ መዛግብቶች፣ ቃለመጠይቆችና ቡድንተኮር ውይይቶች በግብዓትነት ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን  ለንፅፅር ይረዳ ዘንድ የሌሎች አገራት ተሞክሮንም ለመቃኘት ተሞከሯል፡፡ በዚህም መሠረት ጥናቱ ባለሶስት አማራጭ የመፍትሔ ኃሳብ ያቀረበ ሲሆን የመጀመሪያው አሁን ከሕግ አገልግሎት በአገሪቱ እየተሰበሰበ ያለውን የሽያጭ ታክስ እንዳለ በማስቀጠል ለፍትሕ ተደራሽነትና ለሕገመንግስታዊ መብቶች መከበር ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር መወሰድ ያለባቸውን ርምጃዎች አመላክቷል፡፡ በሌላኛው የአማራጭ መፍትሔ ከሕግ አገልግሎት የሚሰበሰበውን የሽያጭ ታክስ ሙሉ በሙሉ በማስቀረት ሌሎች አማራጭ የገቢ ምንጮችን መጠቀም እንደሚቻል ጠቁሟል፡፡ የመጨረሻው የመፍትሔ ኃሳብ ደግሞ ሁኔታዎችን ያገናዘበ ስልት በመቀየስ ለሕግ አገልገሎት ራሱን የቻለ አዲስ ሠንጠረዥ ማዘጋጀትን የሚጠይቅ ነው፡፡ ለዚህም ያግዝ ዘንድ የሕግ አገልግሎቶችን አስፈላጊነትና በሕገመንግስት ጥበቃ ከተደረገላቸው መብቶች ጋር ያላቸውን ቁርኝት፣ የሕግ አገልግሎት ተጠቃሚውን የመክፈል አቅምና የመንግስትን የገቢ ፍላጎት ባገናዘበ መልኩ በሠንጠረዥ በመከፋፈል በተለያዩ የታክስ ምጣኔዎች የሽያጭ ታክስ እንዲሰበሰብ የሚመክር ነው፡፡ 

ጸሐፊ፦ ሙሐመድ ዳውድ አልቃድር 

በ1995 የወጣው የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ ሰዎች በርካታ የሕግ ጥበቃዎችን ያደርጋል፡፡ እነዚህ ጥበቃዎች በዋናነት በሕግ ፊት በእኩል የመታየት፣ በሕግ አግባብ የመዳኘት፣ አላግባብ ቤታቸውና አካላቸው ከመበርበር የመጠበቅ፣ ከሕግ አግባብ ውጭ ያለመያዝ፣ በጠበቃ የመወከል፣ ንፁህ ሆኖ የመገመት፣ የፍርድ ሂደታቸው በግልፅ ችሎት ፈጣን በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የማድረግ፣ የሚቀርብባቸውን ማስረጃ የመመልከትና መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ3፣ ኢሰብአዊ ከሆነና ጭካኔ ከተሞላበት ቅጣት የመጠበቅ እና በአንድ ወንጀል ሁለት ጊዜ ያለመቀጣት መብት ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች በአብዛኛው እድሜያቸው ከ 18 አመት በላይ በሆኑ ወይም ለአካለመጠን በደረሱ ወጣቶች ላይ የሚተገበሩ ሲሆን አካለመጠን ባልደረሱ ሰዎች ላይ ሁኔታው የተለየ ሆኖ ይገኛል፡፡ በወንጀል ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ አዋቂ ሰዎች በሕግ የተቀመጡ ጥበቃዎች አካለመጠን ላልደረሱ ሰዎች ሲከለከሉ ወይም በዝምታ ሲታለፉ ይስተዋላል፡፡

Ethiopia's Education and Training Policy is a comprehensive and coherent policy that aims to provide all Ethiopians with access to quality education. The policy is based on equity, quality, and relevance principles and is designed to promote human and national development. The policy also emphasizes the importance of non-formal education, designed to provide adults with the skills and knowledge they need to participate in the workforce and contribute to society.

 

This article examines the extent of party autonomy in determining the norms that apply to the substance of a commercial dispute in arbitration. Particularly, it analyses ‘principles of law,’ the normative basis for arbitration under Ethiopian law. The article further explores whether parties to the arbitration are at liberty to mandate the application of foreign law, rules of law and equity. It also examines whether a ‘mandate to settle’ is enforceable under Ethiopian law. The article concludes that Ethiopian law allows maximum flexibility to parties as regards to the determination of norms applicable to the substance of a commercial dispute. The law can even be construed as recognising ‘mandate to settle’.

By - Seyoum Yohannes Tesfay

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሕግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ማውጫ ቅጽ 01-25

አዘጋጅ፡ - አረጋይ ገ/እግዚአብሔር (LLB, LLM) የሕግ አማካሪና ጠበቃ

የዚህ ፅሑፍ/ማውጫ ዝግጅት ዓላማ አንድ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሕግ ትርጉም የሰጠባቸው ውሣኔዎች ዝርዝር ማውጫ ሰንጠረዥ አስቀድሞ ከቅጽ 01 እስከ 16 ቀጥሎም ከቅጽ 01 እስከ 24 ተዘጋጅቶ በኢንተርኔት ጭምር የሚገኙ ቢሆንም የተዘጋጁበት አገባብ/መንገድ በጥቅል በዘርፍ ደረጃ (ለምሳሌ ውል) ስለሆነ አንድ ነገር (ለምሳሌ የሽያጭ ውል) ለመፈለግ ጥቅል ዘርፉ በሙሉ ማየት ስለሚያስፈልግ ጥቅል ዘርፉ እዳለ ሆኖ በዛ ዘርፍ ያሉ ውሳኔዎችን በንኡስ ዘርፍ በመለየት/በመከፋፈል ማለት በቅጹ ቀደም ተከተል ሳይሆን በይዘታቸው ተመሳሳይነት ያላቸው ጉዳዮች አንድ ላይ በማምጣት በቀላሉ በመፈለግ ለመጠቀም ያለመ ነው።

ሁለት  ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ ውሳኔዎች (ለምሳሌ የውል፣ ዳኝነት ሥልጣን፣ አፈፃፀም፣ የጉምሩክ ወንጀሎችና ሌሎች ጉዳዮች) ከተቀመጠ ጥቅል ዘፍር ውጪ በሌላ ዘርፍ የሚገኙት ወይም/እና ከሌላ ዘርፍ ተያያዥነት ያላቸው ውሳኔዎች ስላሉ እነዛን ውሳኔዎች ከተቀመጡበት ጥቅል ዘርፍ “ኮፒ ፓስት” በማለት መቀመጥ በሚገባቸው ወይም/እና ተያያዥነት ወዳላቸው ጥቅል ዘርፍ የራሱ አርእስት ተሰጥቶት በድጋሜ እንዲቀመጡ በማድረግ ስለአንድ ዘርፍ በአንድ ላይ እንዲገኙ በማድረግ በቀላሉ በመፈለግ ለመጠቀም ያለመ ነው። ሶስት  በልዩ ልዩ ዘርፍ ያሉ ውሳኔዎች ከጥቂቶቹ ውሳኔዎች በስተቀር ባሉት ጥቅል ዘርፎች መቀመጥ እየተገባቸው ልዩ ልዩ በሚል ዘርፍ ስለተቀመጡ እነዛን ውሳኔዎች የጥቅል ዘርፉ አቀማማጥ ግምት ውስጥ በማስገባት በዛ ልዩ ልዩ በሚል ዘርፍ በንኡስ ዘርፍ ደረጃ ለይቶ/ከፋፍሎ በማስቀመጥ በቀላሉ በመፈለግ ለመጠቀም ያለመ ነው። አራት  በማውጫው ያሉ ብዙ ውሳኔዎች ጥቅል ዘርፉ እንዳለ ሆኖ በንኡስ ዘርፍ ደረጃ ስለምን ጉዳይ መሆናቸው ስለማያሳዩ እነዛ ውሳኔዎች ዋና ምንጭ ከሚባለው ከመፅሓፉ ይዘታቸውን በማየት ጥቅል ዘርፉ ባለበት ቦታ ወደ ሚመለከታቸው ንኡስ ዘርፍ በማስቀመጥ ስለአንድ ንኡስ ዘርፍ በአንድ ላይ እንዲገኙ በማድረግ በቀላሉ በመፈለግ ለመጠቀም ያለመ ነው። አምስት በተለያየ ዘርፍ ያሉ ከማስረጃና የህግ ግምት ጋር የተያያዙ የፍትሐብሔር ጉዳዮች ለብዙ ነገር ያገለግላሉ ተብለው የተመረጡትን “ኮፒ ፓስት” በማለት በድጋሜ በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ዘርፍ በማስቀመጥ በቀላሉ በመፈለግ ለመጠቀም ያለመ ነው።

በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም የተበዳይ ተወካይና ቤተዘመዶች በደል ካደረሰባቸው ሰው ፍትሕን በገዛ እጃቸው ያገኙ ነበር። ተበዳይ ጥቃት ያደረሰበትን ሰው ሲፈልግ ይበቀላል፣ ሲፈልግ በፍርድ አደባባይ ይከሳል ወይም ለደረሰበት በደል ከተበዳይ ከሳ ይቀበላል። አይ ይህን ሁሉ አልፈልግም ካለም ከሁሉም ታቅቦ ፍትሕን ከእግዚአብሔር እየጠየቀ ይኖራል። በዚህ ጊዜ ምርመራ አጣርቶ ክስ የሚመሰርት የዐቃቤ ሕግ ተቋም በሀገሪቱ አልነበረም። በግለሰቦች መሀከል የሚፈጠር አለመግባባቶችን ‹‹የወንጀል›› ጉዳይ እና የግለሰቦች የፍትሐብሔር ጉዳይ ብሎ የሚከፋፍል የሕግ ስርአት ባለመኖሩ ጥቂት በሀይማኖትና በመንግስት ላይ የሚፈፀሙ በአሁኑ ሰአት የፓለቲካ ወንጀል እየተባሉ ከሚጠሩ ወንጀሎች በስተቀር ሁሉም አለመግባባቶች ላይ ግለሰቦች በራሳቸው ከሳሽ በመሆን ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ያቀርባሉ ወይም ፍትሕን በእጃቸው ያገኙ ነበር። ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዱ ከሆነ ክስ የመመስረት፣ የተጀመረን ክስ የሟቋረጥ፣ ቅጣትን በመምረጥ ተበዳይ ግለሰብ ሁሉን አድራጊ ነበር። የወንጀል ይዘት ያላቸው ጉዳዮችን ከፍትሀብሔር ጉዳዮች ጋር በማጣመር የጉዳት ካሳን መጠየቅም ይቻል ነበር። በዘመኑ የወንጀል ተበዳዮች በወንጀል ጉዳይ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች ነበሩ።

አዘጋጆቹ በዚህ ጊዜ በመስፍን ታፈሰ እና ጓዶቹ (MTA) የሕግ ቢሮ በአሶሲየትነት በመስራት ላይ የሚገኙ ሲሆኑ ይህን ስራ አዘጋጆቹ በግላቸው የሰሩት እና የሚሰሩበትን ተቋም ያካተተ ወይም የሚወክል አይደለም። ይህ ማውጫ የሚያገለግለው ለትምህርት እና ለመረጃ ምንጭነት ብቻ ነው። በዚህ ማውጫ ዝግጅት ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያዘጋጀው ከ ቅጽ 1 እስከ 16 ማውጫን በመጠቀም የቀሩትን ቅጾች አጠቃለን አዘጋጅተናል።

አዘጋጆቹ ይህን ማውጫ በሚያዘጋጁበት ጊዜ በውስጡ ያሉትን መረጃዎች እውነታነት ለማረጋገጥ አስፈላጊውን ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ ማውጫ ሲዘጋጅም ትክክለኛ መረጃ እንዲይዝ በማሰብ ነው፡፡ ሆኖም ግን በዚህ ማውጫ ላይ ሊኖሩ በሚችሉ ስህተቶች፣ ግድፈቶች፣ ጉድለቶች እንዲሁም አለመስማማቶች ሊከሰቱ ለሚችሉ ጉዳቶችም ሆነ ኪሳራ አዘጋጆቹ ምንም አይነት ኃላፊነት እንደማይወስዱ ያሳውቃሉ።

ይህ ማውጫ በዋነኛነት የመረጃ ምንጭ እንዲሆን እና ለሕግ ማህበረሰቡ ቀላል እና ፈጣን ማጣቀሻ እንዲሆን የተዘጋጀ ቢሆንም ቀጥታ የባለሞያ ምክር ወይም ድጋፍ አይተካም። ይህን አይነት አገልግሎት ከተፈለገ ከባለሞያ መጠየቅ አለበት፡፡

Federal Supreme Court Cassation Decisions Volume 25
 35324 Downloads
 6.01 MB
 01-20-2023

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቅጽ 25 የሰበር ውሳኔዎችን አትሟል። ውሳኔዎቹን ከዚህ ያግኙ!

CRIMINAL PROCEDURE LAW - PRINCIPLES, RULES AND PRACTICES
 17510 Downloads
 1.7 MB
 11-22-2022

The preparation of this material is to assist teachers in teaching criminal procedure law and to enrich the dialogue for reform. However, in order to make the material useful for others who are in the practice of law, I restrained myself from raising highly academic questions. However, an effort is made to include almost all of the important issues in our criminal process. I came to learn, during my teaching career that students do not get enough materials on the subject included in Part I—the ideal process, the purpose of criminal procedure law, a little bit of economics of criminal justice, and the existing criminal process. They are included in order to better contextualize the criminal process.

Abstract

Construction industry has two opposite prospective factors toward the development. It is widely recognized as being both economically and socially important. Yet it is also considered to be the most hazardous. Global estimates by the International Labor Organization (ILO) show that occupational health and safety (OHS) problems in the construction industry has a disproportionately high rate of recorded accidents. ILO estimates at least 60,000 fatal accidents a year on construction sites around the world, that is one in six of all fatal work-related accidents while global trade union federation puts the figure much higher at 108,000 which is 30% of all work related accidents. In addition, while the cost of all occupational accidents account to 1.25 trillion USD (4%), Occupational injuries and fatalities within the construction industry have been estimated over 10 billion USD annually.

 

Regarding Ethiopian situation, study carried out in 2020 revealed that the highest prevalence of occupational injury was reported from the construction sites which are 50.8%. Different studies that were carried out prior to this 2020 study in specific part of the country, like in Addis ababa, Gonder, Dessie, arba minch, SNNP regional state, etc also shows construction accidents is responsible for 38% ~ 46% of all work related accident. More surprisingly, research has found that 98% of these accidents are preventable. An instrument ever created to control this work related tragedy was implementing OSH rule at work site. Ideally, the implementation of OSH rule can be defined by the state of its legal and institutional framework, the level of the capacities of institutions responsible for OSH rules enforcement, and the degree of its actual implementation and enforcement. Thus, the objective of this paper is to appraise the status of legal and institutional framework to implement OSH rule in Ethiopian construction industry to take stock of the progress made in the industry and identify the remaining challenges ahead in general and its prospects and constraints in particular.

Ethiopia introduced a new Commercial Code in March 2021, replacing the Commercial Code of the Empire of Ethiopia Proclamation No. 166/1960 (the repealed Commercial Code) that governed business operation since 1960. There were many factors that necessitated the revision of the repealed Commercial Code including the demand for responsible corporate management. In Ethiopia, the emergence of publicly held share companies and the rise in the number of shareholders demand to give due emphasis to corporate management. The 1960 Ethiopian Commercial Code failed to provide an adequate legislative response to complex governance issues of the day. Consequently, the Federal government of Ethiopia introduced wide-ranging legal reforms as part of the economic liberalization and modernization. However, the lack of up-to-date legal research and expert commentaries has remained a major challenge to adapt for practice and for the judicial sector. This paper aims to uncover changes under the new Commercial Code of the Federal Democratic Republic of Ethiopia Proclamation No. 1243/2021 (the FDRE Commercial Code) concerning the composition, role, and accountability of the board of directors.

The translation and publication of the Federal Administrative Procedure Proclamation was done by the Ethiopian Lawyers Association in partnership with USAID’s Feteh (Justice) Activity in Ethiopia as part of their efforts to build on the capacity of civil society organizations that are involved in governance and judicial reform efforts. Special thanks goes to the Ethiopian Lawyers Association. 

The translation and publication of the Federal Administrative Procedure Proclamation was done by the Ethiopian Lawyers Association in partnership with USAID’s Feteh (Justice) Activity in Ethiopia as part of their efforts to build on the capacity of civil society organizations that are involved in governance and judicial reform efforts. Special thanks goes to the Ethiopian Lawyers Association. 

The translation and publication of the Federal Administrative Procedure Proclamation was done by the Ethiopian Lawyers Association in partnership with USAID’s Feteh (Justice) Activity in Ethiopia as part of their efforts to build on the capacity of civil society organizations that are involved in governance and judicial reform efforts. Special thanks goes to the Ethiopian Lawyers Association. 

The translation and publication of the Federal Administrative Procedure Proclamation was done by the Ethiopian Lawyers Association in partnership with USAID’s Feteh (Justice) Activity in Ethiopia as part of their efforts to build on the capacity of civil society organizations that are involved in governance and judicial reform efforts. Special thanks goes to the Ethiopian Lawyers Association. 

The translation and publication of the Federal Administrative Procedure Proclamation was done by the Ethiopian Lawyers Association in partnership with USAID’s Feteh (Justice) Activity in Ethiopia as part of their efforts to build on the capacity of civil society organizations that are involved in governance and judicial reform efforts. Special thanks goes to the Ethiopian Lawyers Association.