• መብትና ግዴታዎን ይወቁ - ስለሙስና ወይም ብልሹ አሠራር አጠቋቆም

    የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች አቀራረብ

    የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ - ሙስና ኮሚሽን የሙስና ወንጀልና ብልሹ አሰራርን በተመለከተ ጥቆማዎች የሚቀርቡባቸውን መንገዶች በግልጽ አስቀምጧል፡፡ በዚህ መሠረት ሙስና ወይም ብልሹ አሠራር ተፈጽሟል ብለው የሚያምኑ ከሆነ ከዚህ በሚከተለው መልኩ ማስታወቅ ይቻላል፡፡ 

  • መብትዎን ይወቁ - በፖሊስ መያዝ፣ ማረፊያ ቤት መወሰድ ጋር በተያያዘ

    ፖሊስ ካስቆምዎ

    • ፖሊሱን ማናገር አይጠበቅቦትም፡፡ ሁሉጊዜም ቢሆን ያለመናገር ወይም ዝም የማለት መብት አለዎት፡፡ ያለመናገር ወይም ዝም የማለት መብት ማለት በተጠረጠሩበት ወንጀል ምንም ዓይነት መግለጫ ያለመስጠት መብት ማለት ሲሆን ስምና አድራሻዎትን ወይም ስለማንነትዎ መናገር ግን {tip የወንጀል ሕግ አንቀጽ 807 (ትዕዛዝን አለመፈፀም):: ማንም ስሙን ወይም ማንነቱን እንዲነግር፣ ሥራዎን/ሙያውን፣ መኖሪያ ሥፍራውን፣ አድራሻውን ወይም የግል ሁኔታውን የሚመለከት ማናቸውንም ሌላ ዝርዝር ጉዳይ እንዲገልጽ የሥራ ግዴታውን በሚያከናውን አንድ የመንግሥት ሠራተኛ በአግባቡ ሲጠየቅ ወይም ሲታዘዝ እንቢተኛ የሆነ እንደሆነ ከአንድ መቶ በር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ወር በማይበልጥ የማረፊያ ቤት እሥራት ይቀጣል፡፡}ግዴታዎ{/tip} መሆኑን ያስታውሱ፡፡
  • መብትዎን ይወቁ - እንደ አሠሪ ወይም እንደ ሠራተኛ ያለበዎት ግዴታ

    ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኛ ከሆኑ መሠረታዊ ሕጋዊ መብትና ግዴታ አለበዎት፡፡ ከአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታ ተያይዘው ያሉ መብቶች አጅግ በርካታ ቢሆኑም ዋና ዋና የሚባሉትን ግዴታዎች ቢያወቁ ለርሶ ጠቃሚ ይሆናል በሚል እምነት የአሠሪና ሠራተኛ ግዴታዎች ጠቅለል ባለ መልኩ አቅርበነዋል፡፡

  • ርካሽ ሞባይል መግዛት በወንጀል ሊያስጠይቅዎ እንደሚችል ያውቃሉ?

    አይዞት አይደንግጡ! የገዙት ሞባይል ርካሽ በመሆኑ ብቻ ወንጀለኛ ይሆናሉ ማለታችን አይደለም፡፡ ነገር ግን ከመደበኛ የግብይት ሥርዓት ውጭ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከግለሰቦች በርካሽ ዋጋ የምንሸምታቸው የሞባይል ስልኮች ፍርድ ቤት አስቀርበው በእሥራት ሊያስቀጡን የሚችሉበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም፡፡

  • ሰላማዊ ሰልፍ፣ ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የማድረግ መብትና ግዴታዎ አንዳንድ የሕግ ነጥቦች

    ሰላም እንዴት ናችሁ ውድ የአቢሲኒያሎው ድኅረገጽ ተከታታዮች! ዛሬ ስለሰላማዊ ሰልፍ እና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የማድረግ መብትዎ አንዳንድ የሕግ ድንጋጌዎችን ልንነግራችሁ ወደድን፡፡ መሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን አስመልክቶ በሀገራችን የሚጠቀሱ የሕግ መሠረቶች የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 30 ድንጋጌዎች እና የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 3/1983) ናቸው፡፡

  • ስለቃብድ ምን ያህል ያውቃሉ?

     

    ቃብድ የሚለው ቃል በተለምዶ ቀብድ ብለን የመንጠራው ነው፡፡ ሕጋችን ቃብድ ስለሚለው እኛም ቃብድ ብለነዋል፡፡ ያው እናንተ ቀብድ ብላችሁ ተረዱት፡፡

  • ስለወሳኝ ኩነት ምዝገባ ምን ያህል ያውቃሉ

    ልደትና ሞት ጋብቻና ፍቺ የሰው ልጅ ሕይወት የሚጀመርባቸውና የሚጠናቀቅባቸው እንዲሁም የሚያልፍባቸው የሕይወት ኩነቶች ናቸው፡፡ እንግዲህ ወሣኝ ኩነት በመባል የሚታወቁት የልደት፣ የጋብቻ፣ የፍቺ እና የሞት ክስተቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ክስተቶች ወሣኝ ኩነቶች የተባሉበት ዋናው ምክንያት በየአገሮች ሕገ-መንግሥትና በዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች የታወቁ የሰብዓዊ፣ የማኅበራዊና የፖለቲካ መብቶችን ተፈጻሚ ለማድረግና ለመጠበቅ ወሳኝ የሆኑ ሕጋዊ የግለሰብ ማንነት መረጃዎች ምንጭ በመሆናቸው ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ኩነቶቹ የአንድን አገር ሕዝብ ብዛትና ዕድገትን በትክክል ስለሚያሳዩ፣ ለኅብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባሕላዊ አገልግሎት አሰጣጥ ለሚዘጋጁ ዕቅዶች ዝግጅትና አፈጻጸም እስከ ዝቅተኛው አስተዳደር ክፍል አልፎም በግለሰቦች ደረጃ ተፈላጊና ወሳኝ መረጃዎች በመሆናቸው ወሳኝ ኩነት ተብለዋል፡፡

  • ንጽህናው የተጠበቀ በቂ የመጸዳጃ ቤት ስለማግኘት መብትዎ

    ‹‹መሽናት ክልክል ነው›› ‹‹መሽናት በሕግ ያስቀጣል›› ‹‹አጥር ሥር የሚሸና ውሻ ብቻ ነው›› …ወዘተ በሀገራችን ልዩ ልዩ ቦታዎች የሚገኙ የክልከላ ጥቅሶች ናቸው፡፡ በአብዛኛው የሀገራችን ከተሞች በመንገድ ዳር ሲሸኑ ማየት የተለመደ ድርጊት ከመሆኑ ባሻገር ነውርነቱ ቀርቷል፡፡ በውነቱ ለከተማችን ሽንት ሽንት ማለት ወንዶች ተጠያቂዎች ነን፡፡

  • የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ፋይል ለማስከፈት መሟላት ስለሚኖርባቸው ጉዳዮች

    ሰላም እንዴት ናችሁ! ዛሬ የሰበር ቅሬታ ወይም አቤቱታ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸው ጉዳዮች አጭር ነገር ልናስታውሳችሁ ወደድን፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ጉዳይ በስር ፍርድ ቤት መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በመሆኑም በሰበር ሊታረምልኝ ወይም ሊታይልኝ ይገባል የሚል አንድ አቤቱታ አቅራቢ ማሟላት የሚገባቸው ወይም ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው አቅረበናል፡፡

  • ያከራዩትን ሰው ማንነት አለማሳወቅ ከ3 እስከ 10 ዓመት ጽኑ እሥራት እንደሚያስቀጣ ያውቃሉ?

    ማንኛውንም ቤት፣ ለንግድ ቢሆን ለመኖሪያ፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ የሚያከራዩ ከሆነ ይህንን የሕጉን አንቀጽ ከግምት ያስገቡ፡፡ በ2001 ዓ.ም የወጣው የጸረ ሽብር አዋጅ አዋጅ ቁጥር 652/2001 በአንቀጽ 15 ማንኛውም ቤት፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ ወይም ተመሳሳይ መገልገያ አከራይ (ልብ ይበሉ አከራይ) የሆነ ሰው የተከራዩን ማንነት በዝርዝርና በጽሑፍ የመያዝ እንዲሁም በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የማሳወቅ ግዴታ አለበት ብሎ ደንግጓል፡፡