በደርግ ዘመን አዋጅ ቁጥር 47/67 ተግባራዊ በሆነበት ወቅት ያላግባብ የተወረሱ የግለሰብ ቤቶች አሁን ላይ ለግለሰቦቹ ወይም ለሕጋዊ ወራሾቻቸው ሊመለሱ የሚችሉበት የሕግ አግባብን በተመለከተ ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

የንጉሣዊ ሥርዓት መውደቁን ተከትሎ ወደ መንግሥታዊ ሥልጣን የመጣው ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት የመንግሥት ንብረት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር...

ከውርስ ኃብት ክፍፍል ጋር የተያያዙ አንዳንድ ነጥቦች ከፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከሰጣቸው ውሰኔዎች ጋር በማገናዘብ የቀረበ

የሟች የውርስ ኃብት ተጣርቶ ከተዘጋ በኋላ የውርስ ኃብት ባለቤትነት ወደ ሟች ወራሾች ይተላለፋል፡፡ በመሆኑም ውርስ ከተዘጋ በኋላ ወራሾች መሀከል ክፍያ...

ጠበቃ በጋብቻ ፍቺ ሂደት ስለሚኖረው የሙያ ወሰን እና የሰበር ተቃርኖ

ጋብቻ በሁሉም ባህሎችና ሃይማኖቶች ትልቅ ክብር እና ልዩ ቦታ የሚሰጠው የሃገር ምሶሶ የሆነ የቤተሰብ ተቋም የሚፈጥ ሕጋዊ ኩነት ነው፡፡ በመሆኑም ፀንቶ እንዲቆይ በመንግስት እና በህብረተሰቡ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ መንግስት ጋብቻ ሲመሰረት፣ በጋብቻ ውስጥ እና ሲፈርስ ግንኙነቱ የሚመራበትን ሥነ ስርዓት...

የከተማ መሬት ሕግ በአዲስ አበባ - ክፍል አንድ - የሚል የሕግ መጽሐፌን በማሳተም ለአንባቢያን አቅርቢያለሁ

በመዲናችን የመሬት ሕግ ላይ ትኩረት ያደረገውና ”የከተማ መሬት ሕግ በአዲስ አበባ” የሚል አርዕስት ያለው መጽሐፍ ስለ መሬት ሕግ ጠቅላላ ጽንሰ ሃሳባዊ ጉዳዮችን ጨምሮ ስለ እስከዛሬው የአገራችን የመሬት ስሪት ሁኔታ፣ ከዚሁ ጋር...

Would ‘reception’ look different in Ethiopia if we considered international law a custom rather than a treaty?

Until this day, no scholarly research has squarely dealt with the process of reception of...

የመንግሥትና የግል አጋርነት አዋጅና መመሪያ ይዘት አጭር ማብራሪያ

መንግሥት ብቻውን የሀገሪቱን የመሠረተ ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች ማከናወን የማይችል ከመሆኑ በተጨማሪ የግሉ ዘርፍ በሀገሪቱ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክት ሥራዎች ላይ የራሱን የሆነ...

know your legal rights

  • የሙስና ወንጀል ጥቆማዎች አቀራረብ

    የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ - ሙስና ኮሚሽን የሙስና ወንጀልና ብልሹ አሰራርን በተመለከተ ጥቆማዎች የሚቀርቡባቸውን መንገዶች በግልጽ አስቀምጧል፡፡ በዚህ መሠረት ሙስና ወይም ብልሹ አሠራር ተፈጽሟል ብለው የሚያምኑ ከሆነ ከዚህ በሚከተለው መልኩ ማስታወቅ ይቻላል፡፡ 

  • ፖሊስ ካስቆምዎ

    • ፖሊሱን ማናገር አይጠበቅቦትም፡፡ ሁሉጊዜም ቢሆን ያለመናገር ወይም ዝም የማለት መብት አለዎት፡፡ ያለመናገር ወይም ዝም የማለት መብት ማለት በተጠረጠሩበት ወንጀል ምንም ዓይነት መግለጫ ያለመስጠት መብት ማለት ሲሆን ስምና አድራሻዎትን ወይም ስለማንነትዎ መናገር ግን {tip የወንጀል ሕግ አንቀጽ 807 (ትዕዛዝን አለመፈፀም):: ማንም ስሙን ወይም ማንነቱን እንዲነግር፣ ሥራዎን/ሙያውን፣ መኖሪያ ሥፍራውን፣ አድራሻውን ወይም የግል ሁኔታውን የሚመለከት ማናቸውንም ሌላ ዝርዝር ጉዳይ እንዲገልጽ የሥራ ግዴታውን በሚያከናውን አንድ የመንግሥት ሠራተኛ በአግባቡ ሲጠየቅ ወይም ሲታዘዝ እንቢተኛ የሆነ እንደሆነ ከአንድ መቶ በር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከአንድ ወር በማይበልጥ የማረፊያ ቤት እሥራት ይቀጣል፡፡}ግዴታዎ{/tip} መሆኑን ያስታውሱ፡፡
  • ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኛ ከሆኑ መሠረታዊ ሕጋዊ መብትና ግዴታ አለበዎት፡፡ ከአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታ ተያይዘው ያሉ መብቶች አጅግ በርካታ ቢሆኑም ዋና ዋና የሚባሉትን ግዴታዎች ቢያወቁ ለርሶ ጠቃሚ ይሆናል በሚል እምነት የአሠሪና ሠራተኛ ግዴታዎች ጠቅለል ባለ መልኩ አቅርበነዋል፡፡

  • አይዞት አይደንግጡ! የገዙት ሞባይል ርካሽ በመሆኑ ብቻ ወንጀለኛ ይሆናሉ ማለታችን አይደለም፡፡ ነገር ግን ከመደበኛ የግብይት ሥርዓት ውጭ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከግለሰቦች በርካሽ ዋጋ የምንሸምታቸው የሞባይል ስልኮች ፍርድ ቤት አስቀርበው በእሥራት ሊያስቀጡን የሚችሉበት አጋጣሚ ጥቂት አይደለም፡፡

  • ሰላም እንዴት ናችሁ ውድ የአቢሲኒያሎው ድኅረገጽ ተከታታዮች! ዛሬ ስለሰላማዊ ሰልፍ እና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የማድረግ መብትዎ አንዳንድ የሕግ ድንጋጌዎችን ልንነግራችሁ ወደድን፡፡ መሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን አስመልክቶ በሀገራችን የሚጠቀሱ የሕግ መሠረቶች የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 30 ድንጋጌዎች እና የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 3/1983) ናቸው፡፡

  •  

    ቃብድ የሚለው ቃል በተለምዶ ቀብድ ብለን የመንጠራው ነው፡፡ ሕጋችን ቃብድ ስለሚለው እኛም ቃብድ ብለነዋል፡፡ ያው እናንተ ቀብድ ብላችሁ ተረዱት፡፡

  • ልደትና ሞት ጋብቻና ፍቺ የሰው ልጅ ሕይወት የሚጀመርባቸውና የሚጠናቀቅባቸው እንዲሁም የሚያልፍባቸው የሕይወት ኩነቶች ናቸው፡፡ እንግዲህ ወሣኝ ኩነት በመባል የሚታወቁት የልደት፣ የጋብቻ፣ የፍቺ እና የሞት ክስተቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ክስተቶች ወሣኝ ኩነቶች የተባሉበት ዋናው ምክንያት በየአገሮች ሕገ-መንግሥትና በዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች የታወቁ የሰብዓዊ፣ የማኅበራዊና የፖለቲካ መብቶችን ተፈጻሚ ለማድረግና ለመጠበቅ ወሳኝ የሆኑ ሕጋዊ የግለሰብ ማንነት መረጃዎች ምንጭ በመሆናቸው ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ኩነቶቹ የአንድን አገር ሕዝብ ብዛትና ዕድገትን በትክክል ስለሚያሳዩ፣ ለኅብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባሕላዊ አገልግሎት አሰጣጥ ለሚዘጋጁ ዕቅዶች ዝግጅትና አፈጻጸም እስከ ዝቅተኛው አስተዳደር ክፍል አልፎም በግለሰቦች ደረጃ ተፈላጊና ወሳኝ መረጃዎች በመሆናቸው ወሳኝ ኩነት ተብለዋል፡፡

  • ‹‹መሽናት ክልክል ነው›› ‹‹መሽናት በሕግ ያስቀጣል›› ‹‹አጥር ሥር የሚሸና ውሻ ብቻ ነው›› …ወዘተ በሀገራችን ልዩ ልዩ ቦታዎች የሚገኙ የክልከላ ጥቅሶች ናቸው፡፡ በአብዛኛው የሀገራችን ከተሞች በመንገድ ዳር ሲሸኑ ማየት የተለመደ ድርጊት ከመሆኑ ባሻገር ነውርነቱ ቀርቷል፡፡ በውነቱ ለከተማችን ሽንት ሽንት ማለት ወንዶች ተጠያቂዎች ነን፡፡

  • ሰላም እንዴት ናችሁ! ዛሬ የሰበር ቅሬታ ወይም አቤቱታ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸው ጉዳዮች አጭር ነገር ልናስታውሳችሁ ወደድን፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ጉዳይ በስር ፍርድ ቤት መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በመሆኑም በሰበር ሊታረምልኝ ወይም ሊታይልኝ ይገባል የሚል አንድ አቤቱታ አቅራቢ ማሟላት የሚገባቸው ወይም ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው አቅረበናል፡፡

  • ማንኛውንም ቤት፣ ለንግድ ቢሆን ለመኖሪያ፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ የሚያከራዩ ከሆነ ይህንን የሕጉን አንቀጽ ከግምት ያስገቡ፡፡ በ2001 ዓ.ም የወጣው የጸረ ሽብር አዋጅ አዋጅ ቁጥር 652/2001 በአንቀጽ 15 ማንኛውም ቤት፣ ቦታ፣ ክፍል ወይም ተሽከርካሪ ወይም ተመሳሳይ መገልገያ አከራይ (ልብ ይበሉ አከራይ) የሆነ ሰው የተከራዩን ማንነት በዝርዝርና በጽሑፍ የመያዝ እንዲሁም በአቅራቢያው ላለ ፖሊስ ጣቢያ በሃያ አራት ሰዓት ውስጥ የማሳወቅ ግዴታ አለበት ብሎ ደንግጓል፡፡