በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 97 መሠረት ኤግዚቢት ወይም ከወንጀል አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ወንጀል የተፈጸመበት ወይም ወንጀል ለመፈጸም በመሣሪያነት የዋሉ ቁሶች (ነገሮች) እንዴት ሊቀመጡና በማስረጃነት ሊያገለግሉ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡
በዚሁ መሠረት ኤግዚቢቶች ላይ የፍርድ ቤት መዝገብ ሹም ቁጥርና ምልክት አድርጎባቸው በተጠበቀ ስፍራ ሊያስቀምጣቸው እንደሚገባና ከተቀመጡበት ስፍራም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንደማይወጡ ተመልክቷል፡፡ ሆኖም በተግባር ፍርድ ቤቶች በወንጀል ጉዳዮች በኤግዚቢትነት የሚያዙ ንብረቶችን ተቀብለው አይመዘግቡም በተጠበቀ ስፍራም አያስቀምጡም፡፡