- በዓመት ከ1800 ብር በላይ ቤት የሚያከራይ አከራዮች ሁሉ የኪራይ ግብር ገቢ የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
- ግብር የማይከፍል ወይም አሳንሶ ገቢውን የማያሳውቅ አከራይን ለገቢዎች በማስረጃ የጠቆመ ተከራይም ሆነ ሌላ ሰው የማበረታቻ ሽልማት አለው።
- ከአከራዮች የሚፈለገው የኪራይ ግብር አሰላልና መጠኑ ምን ይመስላል?
- በዓመት ከ1800 ብር በላይ ቤት የሚያከራይ አከራዮች ሁሉ የኪራይ ግብር ገቢ የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
- ግብር የማይከፍል ወይም አሳንሶ ገቢውን የማያሳውቅ አከራይን ለገቢዎች በማስረጃ የጠቆመ ተከራይም ሆነ ሌላ ሰው የማበረታቻ ሽልማት አለው።
- ከአከራዮች የሚፈለገው የኪራይ ግብር አሰላልና መጠኑ ምን ይመስላል?
በዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ክፍያን ከሚያሳልጡ አሠራሮች መካከል አንዱ የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ነው፡፡ አንድ የባንክ ደንበኛ በባንኩ ውስጥ በከፈተው ሒሳብ ያጠራቀመውን ገንዘብ ለማውጣት የቁጠባ ሒሳብ ደብተሩን መያዝ፣ የባንክ ባለሙያን ማነጋገር፣ ገንዘብ ወጪ ለማድረግ የሚያስችል ፎርም መሙላት፣ ወረፋ መጠበቅ ወዘተ. አይጠበቅበትም፡፡ በደንበኛውና በባንኩ መካከል በሚፈጸም የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ውል ከባንኩ ካርዱንና የሚስጥር ቁጥሩን በመቀበል ባንኩ በተለያዩ ቦታዎች ካስቀመጣቸው የኤቲኤም ማሽኖች አገልግሎት ማግኘት ይችላል፡፡ በአገራችን ይህ አሠራር በተግባር ላይ ከዋለ የተወሰኑ ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ በጣም ውሱን ከሆኑ ጀማሪ ባንኮች በስተቀር በሁሉም የግልና የመንግሥት ባንኮች ተፈጻሚ ሆኗል፡፡ የኤቲኤም ካርድን መጠቀም የራሱ የሆኑ ጥቅሞች እንዳሉት የታመነ ቢሆንም፣ የተወሰኑ በአጠቃቀም ወቅት የሚስተዋሉ ችግሮች እንዳሉ ብዙ ሰው የሚያውቀው ነው፡፡ የኤቲኤም ካርድ በአንዳንድ ማሽኖች ተቀባይነት አለማግኘቱ፣ አንዳንዶቹ ፈጽሞ የማይሠሩ (Active ያልሆኑ) መሆናቸው፣ በአንድ ቀን ማውጣት የሚቻለው የገንዘብ መጠን መወሰኑ፣ የኔትወርክ አለመኖርና ተደጋጋሚ የማሽን ብልሽት፣ በቂ የክፍያ ማሽኖች በየቦታው አለመኖራቸው፣ በኤቲኤም አሠራር የሚታዩ ግድፈቶች ወዲያው ሊታረሙ አለመቻላቸው ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው፡፡ በዚህ ጽሑፍ የምንመለከተው ግን ከባንኩ ውጭ በሆኑ ምክንያቶች በኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ላይ ከተጋረጡ ችግሮች ዐቢይ የሆነውን የካርድ መጥፋት ጉዳይ ነው፡፡
በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል የሚፈረም የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ውል ደንበኞች ካርዳቸውን ወይም የሚስጥር ቁጥራቸውን ለሦስተኛ ወገን አሳልፈው እንዳይሰጡ፣ ካርዳቸውን እንዳይጥሉ፤ ይህ ካልሆነ ግን ካርድ በመጥፋቱ፣ ወደ ሦስተኛ ወገን በመተላለፉ ወይም የሚስጥር ቁጥሩ በመገለጡ ምክንያት ለሚመጣው ጉዳት ደንበኞቹ ኃላፊ ሊሆኑ እንደሚገባ ነው፡፡ የኤቲኤም ካርድ በጠፋ ጊዜም ግን ባንኮች ኃላፊነት ሊኖርባቸው የሚችልበት ሁኔታ ዝግ አይደለም፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በ17ኛ ቮልዩም አስገዳጅ የሕግ ትርጓሜ ከሰጠባቸው ጉዳዮች ውስጥ የሰበር መዝገብ ቁጥር 96309 አንዱ ሲሆን፣ በዚህ ጽሑፍ ይህን አስተማሪ ፍርድ መነሻ በማድረግ አጠር ያለ ዳሰሳ ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡
የጉዳዩ አመጣጥ
ጉዳዩ የጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት ሲሆን፣ ከሳሽ አቶ ዓለማየሁ ግርማ ተከሳሽ ደግሞ ዳሸን ባንክ ነው፡፡ ደንበኛው በባንኩ የቁጠባ ሒሳብ ተጠቃሚ ሲሆኑ፣ የቁጠባ ሒሳባቸውን በኤቲኤም ካርድ ያንቀሳቅሳሉ፡፡ ጥር 23 ቀን 2003 ዓ.ም. የደንበኛው የኤቲኤም ካርድ ይጠፋል፤ ደንበኛውም መጥፋቱን ጥር 25 ቀን 2003 ዓ.ም. በጽሑፍ ለባንኩ ያሳውቃሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባንኩ የኤቲኤም ሒሳባቸውን ባለመዝጋቱ ሪፖርት ከተደረገበት ቀን ጀምሮ እስከ የካቲት 9 ቀን 2003 ዓ.ም. ባንኩ ለማይታወቁ ሦስተኛ ወገኖች ብር 40,300 በኤቲኤም ክፍያ ይፈጽማል፡፡ በዚህ ጊዜ ነው ደንበኛው ባንኩ ሒሳቤን መዝጋት ሲገባው ባለመዝጋቱ ያለፈቃዳቸው ወጪ ለተደረገው ገንዘብ ወለድና ወጪ ባንኩ ኃላፊ እንዲሆን ክስ ያቀረቡት፡፡
Various international, regional and domestic laws imposes obligation on the state to respect and protect fundamental human right and freedom. Stated otherwise, government has the duty respect and protect fundamental rights of its subject. Protecting and respecting these fundamental rights of its subject is internationally and regionally recognized principle.
The same principle hold true in domestic law including our country Ethiopia. FDRE constitution under its art 13(1) provides that “All Federal and State legislative, executive and judicial organs at all levels shall have the responsibility and duty to respect and enforce the provisions of this Chapter”. As per this provision, all organs of the government be it federal and regional are duty bound to respect and enforce the provisions concerning fundamental right including the right to life. Moreover, they are under the duty to ensure the observance of the constitution and the duty to obey. In this respect, art 9(2) FDRE constitution stipulate that “state that all citizens, organ of the state, political organization, other association, as well as their official have the duty to ensure the observance of this constitution and obey it.”
However, none of these human rights are absolute and without limitation. Thus, none of human right may be applauded without limitation and absolutely and hence, be restricted.
In accordance with international human rights law there are essentially two ways in which the State put aside this international obligation. In other word, there are exceptional circumstance in which state restrict fundamental rights of its citizen. These are limitation and. Derogations.
Thus, this piece examines the status of the right to life as far as derogation of human rights is concerned under FDRE constitution. In doing so, the distinction between limitation and derogation will be put. Some international and regional human right instruments will also be dealt with.