ሰበር በአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ሥልጣን ላይ ያሰመረው ቀጭን መስመር

 

የአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣናቸውን የተመለከቱ የተለያዩ ክርክሮች ተነስተዋል፡፡ ዋናው ክርክር በተቋቋመበት ወቅት የተነሳው የሕገ መንግሥታዊነት ጭብጥ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 78 እስከ 80 የዳኝነት አካሉን ሲያዋቅር በተለያዩ ደረጃዎች ያሉት የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚቋቋሙ በመግለጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚወሰዱ ጊዜያዊና ልዩ ፍርድ ቤቶች እንደማይቋቋሙ ደንግጓል፡፡

ይህን መሠረት አድርገው አንዳንዶች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የተቋቋመው የከተማ ነክ ፍርድ ቤት (አሁን የከተማ ፍርድ ቤት) ሕገ መንግሥታዊ አይደለም ሲሉ ሞግተዋል፡፡ የፍርድ ቤቱን ሕገ መንግሥታዊነት የሚደግፉ ወገኖች ደግሞ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 49 በአዲስ አበባ የራስ አስተዳደር ስለፈቀደ አዲስ አበባ እንቅስቃሴዎቿን ለመከታተል የሕግ አውጭ፣ የሕግ አስፈጻሚ እንዲሁም የሕግ ተርጓሚ አካላትን ማቋቋም ትችላለች ብለዋል፡፡ የግራ ቀኙን የሕገ መንግሥታዊነት ለመደገፍ ሌሎችም ምክንያቶች ተጠቅሰዋል፡፡ ያም ሆኖ የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት በአዋጅ ተቋቁሞ መደበኛ የፍርድ ቤት ሥራዎችን መሥራት ከጀመረ ሁለት አሠርት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ሥልጣኖች ተሰጥተውታል፡፡ በተቋቋመበት ወቅት በዋናነት የከተማ አስተዳደሩ የሚያከናውናቸው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የአስተዳደርና የቁጥጥር ሥልጣኖችን ከማስፈጸም ጋር የተያያዙ ክርክሮችን ይመለከት ነበር፡፡ ሁከት ይወገድልኝ፣ ደንብ መተላለፍ፣ ከቀበሌ ቤቶች ጋር የተያያዙ ክርክሮች፣ ከመሬት ጋር የተያያዙ ክርክሮችን ተቀብሎ እንዲያስተናግድ ተፈቀደለት፡፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ ደግሞ ከመሬት ጋር የተያያዙት ጉዳዮች በአስተዳደሩ ስም ለተቋቋመ ቦርድ የተሰጠ ሲሆን፣ በምትኩ ጊዜ ቀጠሮ፣ እስከ አምስት ሺሕ ብር የሚደርሱ የፍትሐ ብሔር ክርክሮች፣ የስም ለውጥ፣ የወራሽነት የምስክር ወረቀት፣ የመጥፋት ውሳኔ፣ የባልና የሚስትነት፣ የሞግዚትነት የምስክር ወረቀት የመስጠት ሥልጣን በተሻሻሉ አዋጆች እንዲሠራ ተደርጓል፡፡

ለፍርድ ቤቱ በተለያዩ ጊዜያት ከተሰጡት ሥልጣኖች ለመረዳት የሚቻለው ፍርድ ቤቱ እንዲሠራቸው የተፈለጉት ክርክሮች ውስብስብነት የሌላቸው፣ በአጭር ጊዜ ሊጠናቀቁ የሚገባቸው፣ የገንዘብ መጠናቸው አነስተኛና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን (Municipality activities) መሠረት አድርገው የሚነሱ ክርክሮችን ነው፡፡

Continue reading
  11837 Hits

ስለ እንደራሴ (ውክልና) ሕግ አንዳንድ ነጥቦች

 

 ውክልናን የተመለከተው ሕግ በአገራችን በብዛት ስራ ላይ ከሚውሉ የሕግ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የፍትህብሄር ሕግ ቁጥር 2199 ውክልናን እንደተረጐመው “ውክልና ማለት ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ህጋዊ ሥራዎች በወካዩ ሥም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ማለት ነው” ይላል፡፡ ከትርጉሙ ለመረዳት እንደምንችለው ውክልና የሚደረገው በወካይና በተወካይ መካከል ሲሆን በውክልናው የሚከናወኑት ስራዎች ህጋዊ መሆን አንዳለባቸው ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ህጋዊ ባልሆኑ ነገሮች ላይ የሚደረግ ውክልና ተቀባይነት የለውም  ማለት ነው፡፡ በሰፊው ስንመለከት ሁለት አይነት ውክልናዎችን እናገኛለን፡፡ እነሱም በፍተሃብሄር ሕግ ቁጥር 2189 ላይ የተቀመጠው ፍፁም የሆነ እንደራሴነት /disclosed or complete  agency/ እና በዚሁ ሕግ ቁጥር 2197 ላይ የተቀመጠው እንደራሴው በራሱ ስም ተግባሮችን የሚፈፅምባቸው የውክልና አይነት/undisclosed agency/ ናቸው:: ለዚህ ፅሁፍ አላማ ግን  የመጀመሪያው አይነት ውክልና ማለትም ፍፁም የሆነውን የእንደራሴነት አይነት እንመለከታለን፡፡ ይህም በፍትሃብሄር ህጉ ቁጥር 2199-2233 ድረስ ያሉትን የህጉን አንቀጾች የተመለከተ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ ፅሁፍ ውስጥየውክልና አስፈላጊነት፣ የውክልና ምንጮች ፣ የውክልና አመሰራረት፣ የውክልና አይነቶች፣ የውክልና ግብ ፣ የተወካይና የወካይ ግዴታዎች፣ ውክልና የሚቋረጥበት ሁኔታ፣ ከውክልና መመሰረት ጀምሮ በውክልና አማካኝነት የሚከናወኑ ተግባሮችና ውጤቶቻቸው ድረስ ወካይ፣ ተወካይና የውክልና ማስረጃውን የሚሰጡ አካሎች ሊያደርጓቸው የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የሚዳሰሱ ይሆናል፡፡

 

1.  ውክልና ለምን ያስፈልጋል?

አንድ ሰው አንዳንድ ተግባሮችን በራሱ ከማድረግ ይልቅ ሌላን ሰው በመወከል ተግባሮቹ እንዲከናወኑለት ይፈልጋል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የጊዜ ጥበት፣ የቦታ ርቀት ወይም የሁኔታዎች አለመመቻቸት፣ የእውቀት ወይም የክህሎት አለመኖርና የችሎታ ማነስ ዋናዋናዎቹ ሲሆኑ ሌሎችም በምክንያትነት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ 

Continue reading
  27963 Hits
Tags:

 አንድ አንድ ነጥቦች ስለ ቼክ እና በተግባር የሚያጋጥሙ የሕግና የአሰራር ችግሮች

 

መግቢያ   

ቼክ በተግባር በሰፊው ከሚሰራባቸውና በሕግ ከተቀመጡት ንግድ ሰነዶች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡  በቼክ ላይ እምነት የሚታጣበት ከሆነ የንግድ ዝውውር ደህንነት (security of transaction) ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ የንግድ ሥራው እያደገ በመጣ ቁጥር በቼክ የሚደረጉ የንግድ ልውውጦች የሚጨምሩ እንደሚሆን የሚታመንና በተግባርም የሚታይ ነው፡፡ የቼክ ዝውውር እየጨረ እንደመጣም መገመት አያዳግትም፡፡ እየጨመረ የመጣውን የቼክን ዝውውር አስተማማኝነት ለማሳደግ ሕጎች ሥርዓቱን ሊቆጣጠሩት ይገባል፡፡ በዚህም መሠረት በእኛ ሀገር የንግድ ሕጉ እና የወንጀል ሕጉ ይህንኑ የቼክ ጉዳይ በዋናነት ይህን ሥርዓት ዘርግተው ይገኛሉ፡፡ ባብዛኛው የቼክ ጉዳይ የሚያከራክር ጉዳይ የሌለበት ቢሆንም አልፎ አልፎ ግን አከራካሪ ጉዳዮች መታየታቸው አልቀረም፡፡ ይህ ጽሑፍ ዓላማውም በቼክ ዙሪያ ያሉትን አስፈላጊ የሕግ ድንጋጌዎችንና አስገዳጅ የፍርድ ውሳኔዎችን ማሳወቅና በተወሰነ መልኩም ቢሆን ለአከራካሪ ጉዳዮች የጸሐፊውን እይታ ማንፀባረቅ ነው፡፡

ቼክ ምንድ ነው?

በንግድ ሕጉ ላይ የቼክ ዓይነቶች፡ የስርዝ ምልክት ያለበት ቼክ (crossed cheque)፣ ከሂሳብ ውስጥ የሚገባ ቼክ (cheques payable in account) እንዲሁም የመንገድ ቼክ(travellers cheque) የሚባሉ ሲኖሩ የዚህ ጽሑፍ ትኩረት ግን እነዚህን ወደ ጎን በመተው በንግድ ሕጉ ቁጥር 827 ጀምሮ የተቀመጠውን መደበኛ የቼክ ዓይነት ላይ ያተኩራል፡፡

Continue reading
  21303 Hits
Tags:

በኢትዮጵያ አሠሪና ሠራተኛ ሕግ የሥራ ስንብት ክፍያ ምንነትና የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮች

 

እንደ መነሻ

የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት ለረጅም ጊዜ በተለያዩ የኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አተሰሳሰቦች የነበረ፤ ያለ እና የሚኖር መስተጋብር ነው፡፡

ታሪኩንም በወፍ በረር መለስ አድርገን ስንመለከት ከካፒታሊስታዊ ሥርዓተ ማኅበር በፊት በነበሩት ሥርዓቶች በተለይም በባሪያ አሳዳሪ /slave-owning/ ሥርዓተ ማኅበር እና በፊውዳል /feudal system/ ሥርዓተ ማኅበር ወቅት ይሰተዋል የነበረው ሠራተኛው እንደ ጪሰኛ የሚቆጠርበት ሥርዓት ነበር፤ የሚያገኘው ጥቅምም ከአሠሪው ምግብ እና መጠለያ እንጂ መደበኛ ደምወዝ አልነበረውም፡፡

የአሠሪና ሠራተኛ ሕግ ብቅ ማለት የጀመረው በኢንዲስትሪ አብዮት ወቅት ሲሆን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትም ከትናንሽ የጎጆ ኢንዱስትሪ ወደ ትላላቅ ፍብሪካዎች በተሸጋገረበት ጊዜ ነበር፡፡ በአንጻሩ አሠሪዎች ደግሞ በቀላሉ ሠረተኛ ቀጥረው ያሠሩ ነበር ለምን ቢባል በወቅቱ በጣም ርካሽ የሰው ኃይል ስለነበር ነው፡፡ በወቅቱም የሠራተኛች አንገብጋቢ ጥያቄ የነበረው የተሻለ የሥራ ሁኔታ /minimum working condition/ እንዲሁም ከሠራተኛ ማኅበር አባልነት ጋር የተያያዙ መብቶች ነበሩ፡፡

Continue reading
  42247 Hits

ሰበር ለመታረቅ በተደረገ ስምምነት ላይ የያዘው አቋም ሲፈተሽ

 

ኢትዮጵያ ውስጥ የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው ፍርድ ቤቶች ብቻ አይደሉም፡፡ ይህን ሥልጣን የተጎናፀፉ ብዙ አካላት አሉ፡፡ ለአብነት ያህል ለመጥቀስ፡- በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ውስጥ የሚገኘው የአስተዳደር ፍርድ ቤት ከሥራ መሰናበት፣ ደመወዝ መቁረጥና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች አስመልክቶ በመንግሥት ሠራተኛውና  በፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤት መካከል የሚነሳ አለመግባባት ላይ ዳኝነት ይሰጣል፡፡ ሕገ መንግሥቱን መተርጎም ላይ አለመግባባት ከተፈጠረ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው፡፡ በግብር ጉዳዮች ላይ የግብር ይግባኝ ሰሚ ኮሚሽን የዳኝነት ሥልጣን አለው፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና መብትና ጥቅም  ጥያቄዎች ላይ የዳኝነት ሥልጣን ለማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ተሰጥቷል፡፡ የከተማ ቦታ ማስለቀቅና የካሳ ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ሥልጣኑ በየከተማ አስተዳደሮች ለሚቋቋሙ ጉባዔዎች ተሰጥቷል፡፡ የንግድ ውድድር ጨቋኝ የሆኑ ድርጊቶችና ያልተገባ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ደግሞ ዳኝነት የሚሰጥ የንግድ አሠራርና የሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን የሚባል ተቋም አለ፡፡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶችም አሉ፡፡ ይሁን እንጂ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያለውን የዳኝነት ሥልጣን ያህል የተጎናፀፈ ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ለማለት ያስደፍራል፡፡ የዚህን ችሎት የዳኝነት ሥልጣን ሊወዳደር ወይም ሊበልጥ የሚችል ፍርድ ሰጪ አካል ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ፣ የሕገ መንግሥት ትርጓሜ ላይ ዳኝነት የመስጠት ሥልጣን ያለው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ብቻ ነው፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የዳኝነት ሥልጣን ያላቸው አካላትን በሙሉ የፍርድ ሰጪነት ሥልጣናቸውን ሲጠቀሙ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለመፈጸማቸውን ይቆጣጠራል፡፡ በተጨማሪ ይህ ችሎት አንድ የሕግ ድንጋጌን የተረዳበት ወይም የተረጎመበት መንገድ ሁሉም የሥር ፍርድ ቤቶች ሊከተሉ ይገባ ዘንድ ግዴታ አለ፡፡ ማለትም፣ ፍርድ ቤቶችና ሌሎች ፍርድ ሰጪ አካላት የሰበር ችሎቱ አንድን የሕግ ድንጋጌ ከተረጎመበት ውጪ አፈንግጠው የራሳቸውን ትርጉም መስጠት አይችሉም፡፡ ስለዚህ የሰበር ችሎቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ፍርድ ሰጪ አካላት ውስጥ ቁንጮ ላይ የሚቀመጥና የዳኝነት ሥርዓቱ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነ ተቋም ነው፡፡

ሰፊ ሥልጣን ሲኖር ደግሞ ሊነጠል የማይችል አብሮ የሚመጣ ግዴታ አለ፡፡ ሰፊ ሥልጣን በጠለቀ ዕውቀት፣ ገደብ የለሽ አስተዋይነትና ሰባዊነት መታጀብ አለበት፡፡ የዜጎች ነፃነት፣ ሕይወትና ደስተኝነት ላይ ተፅዕኖ የመፍጠር ሥልጣን የተሰጠው አካል ሁሉ ሥልጣኑን ሲጠቀም የመጠቀ ዕውቀት፣ የመተንተን ክህሎት፣ አስተዋይነትና ሰባዊነት በማይነጣጠል ሁኔታ ማንፀባረቅ አለበት፡፡ የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት ሰፊ የዳኝነት ሥልጣን ቢጎናፀፍም የጠለቀ የሕግ ዕውቀት፣ ትንታኔ እና መርማሪነት ግን በውሳኔዎቹ ማንጸባረቅ የቻለ መስሎ አይታይም፡፡ ይህ ደግሞ በራሱ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማይካድ ሀቅ ነው፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ተገኔ ጌታነህ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ውሳኔዎች ይዞ በሚወጣው ቅጽ 15 መግቢያ ላይ ‹‹አልፎ አልፎ በውሳኔዎች ጥራትና ሥርጭት ሊታዩ የሚችሉ ችግሮች ሥርዓቱ እየተጠናከረ ሲሄድ የሚፈቱ ሲሆን፣ እነዚህን ችግሮች ለማቃለል እኛም ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ጥረታችን ሊሳካ የሚችለው በውሳኔዎች ላይ በሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ገንቢ የሆኑ ትችቶችና አስተያየቶች ሲቀርቡ ነው፤›› ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

በዚህ ጽሑፌ አንድ ጭብጥን አስመልክቶ የሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ ሌላው ቀርቶ ጀማሪ የሕግ ተማሪዎች የሚማሩበት መጽሐፍ ላይ በቀላሉ የሚገኝ ዕውቀትን ማንፀባረቅ እንዳልቻለ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡ ጭብጡን አስመልክቶ የዛሬ ስምንት ዓመት በብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያና በዘላቂ ግብርና ተሃድሶ ኮሚሽን ጉዳይ ላይ (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ቅጽ 7 ገጽ 148 ይመልከቱ) የሰጠውን ውሳኔ አሁን ደግሞ በቅርቡ በቦሮ ትራቭል የግንባታ ሥራዎች ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበርና በአቶ ኤፍሬም ሽብሩ ጉዳይ ላይ ደግሞ ደግሞታል፡፡ (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ቅጽ 17 ገጽ 358 ጀምሮ ይመልከቱ)፡፡

Continue reading
  7683 Hits

የኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ከአዲስ አበባ ምን ሊሆን ይችላል

 

በሀገራችን በቅርብ ጊዜየቶች ውስጥ በተደጋጋሚ እየተነሱ ከሚገኙ ጉዳዮች እና የሕግ እና የፓለቲካ ተዋንያንን እያነጋገር ያለው አንዱ ጉዳይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከአዲስ አበባ ከተማ ሊኖረው ይገባል በሚል በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 49 (5) የተቀመጠውን ልዩ ጥቅም የተመለከተው ድንጋጌ ነው፡፡በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተቀመጠውን ድንጋጌ አንዳንድ ሰዎች እንደሚያነሱት በሀገሪቷ ውስጥ ያሉትን ሰለማዊ የሆኑ ህዝቦች አብረው ሲኖሩ የነበሩትን ግንኙነት ለማበላሸት እና ልዩነትን ለማጉላት በሚል የተቀመጠ ድንጋጌ አድርገው የሚመለከቱ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ይህ ድንጋጌ በሀገሪቷ ውስጥ የነበረውን ተጨባጭ የህዝቦች ችግር ለመፍታት በሚል የገባ ችግር ፈቺ እና ምክንያቲያው ድንጋጌ እንደሆነ አድርገው ይገልጹታል፡፡ በዚህ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ላይ ሕገ-መንግሥቱ ለሕገ-መንግሥት አርቃቂ ጉባኤ ቀርቦ በሚታይበት ወቅትም ቢሆን የተለያዩ ሀሳቦች የተነሰቡት እና በሃላም ላይ ድንጋጌው ተቀባይነት አግኝቶ የጸደቀበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተደነገገው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ አለው የሚለው ድንጋጌ ይዘት ላይ ምን እንደሆነ እና ምን እንዳልሆነ፤ እነዚህን ልዩ ጥቅሞች በስራ ላይ ለማዋል በሚታሰብበት ውቅት ታሳቢ ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጉዳዮች በመግለጽ ለውይይት የሚሆን መነሻ ሀሳብ ማቅረብ ነው፡፡

የኦሮሞ ህዝብ የብዙ ሺህ ዘመናት አኩሪ ታሪክ ያለው፤ ዘመናው የዲሞክራሲ እሴቶች የሆኑ የመንግሥት አመራር እና አስተዳደር የነበራቸው፤ የራሱ የዘመናት አቆጣጠር፤ አኩሪ ባህላዊ እሴቶች ያሉት ህዝብ ነው፡፡ይህ ህዝብ እንደማናኛውም ህዝብ የነበረው ስልጣኔ እየወደቀ እየተነሳ፤ ከሌሎች ጎረቤት ህዝቦች ጋር ሰላማዊ የሆነ ተቻችሎ የመኖር ባህሪያቶችን ይዞ የኖረ እና እየኖረ የሚገኝ ህዝብ ነው ቢሆንም የራሱን ባህል፤ ቋንቋ ታሪክ እና ሌሎች የማንነት መገለጫዎች እንደ ሃላ ቀር በመቅጠር በፊት የነበሩት የንጉሳዊያን አስተዳደሮች በህዝቡ ላይ እጅግ አሳዛኝ እና ታሪክ ሊረሳው የማይችል ድርጊት ሲፈጽሙ ቆይተዋል፡፡ሕዝቡ ሲፈጸሙበት የነበሩትን ድርጊቶች አንዳንዴ በተደራጃ እና በአብዛኛው በተበታተነ መልኩ ሲታገል እና ሲቃወም ቆይቶ ራሱ በላካቸው ወኪሎቹ መሰረት በ1987 ዓ.ም የጸደቀውን የኢፌደሪ ሕገ-መንግሥት የክልል ባለቤት ሊሆን ችሎዋል፡፡ ህዝቡ የራሱ የሆነ ክልል እንዲኖረው ማድረጉ ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች እና የተለያዩ ክልላዊ አስተዳደሮች ጋር ሊኖረው ስለሚገባው ግንኙት ምን መምሰል እንዳበት በሕገ-መንግሥቱ ላይ ደንግጎዋል፡፡ በዚህ አግባብ በሕገ-መንግሥቱ ላይ ከተቀመጡት መሰረታዊ ጉዳዮች አንዱ ክልሉ ከአዲስ አበባ ከተማ ላይ ልዩ ጥቅም ሊኖረው የሚገባ እንደሆነ የሚያስቀምጠው ድንጋጌ አንዱ ነው፡፡በሕገ-መንግሥቱ ላይ የተቀመጠው ፌደራላዊ ስርዓት መሰረታዊ እምነቱ ብዙሀነትን ማዕከል ያደረግ አንድነትን መፍጠር እንደሆነ በመግቢያው ላይ ደንግጎዋል፡፡

ሕገ-መንግሥቱ ላይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ላይ አለው የሚለው ድንጋጌ ልዩ ጥቅም የሚባሉ ሊጠበቅላቸው/ሊንጸባረቅባቸው የሚገቡ ጉዳዮች ምን እንደሆነ ያመለከተ እንጅ ልዩ ጥቅም ለሚለው ሀረግ የሰጠው ትርጉም የለም፡፡ ልዩ ጥቅም የሚለውን ሀረግ ሲታይ ልዩ የሚለው ቃል ከአንድ ነገር ጋር የተያያዘ እና ከተለመደው ወጣ ያለ የሚለውን ሁኔታ የሚገልጽ ሲሆን ጥቅም የሚለው ደግሞ ህጋዊ ተቀባይነት ያለው አንድ ጉዳይ ላይ ሊኖር የሚችለውን መብት የሚመለክት እንደሆነ ሊወሰድ ይችላል፡፡ስለሆነም ክልላዊ መንግሥቱ  በአዲስ አበባ ላይ ልዩ ጥቅም አለው ሲባል ተለይቶ የሚታወቅ ሕገ-መንግሥታዊ መብት የሚያጎናጽፍ ጥቅም አለው ተብሎ ይወሰዳል፡፡

ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 49 ላይ ለክልሉ መንግሥት ልዩ ጥቅም በአዲስ አበባ ላይ እንዲጠበቅ የፈለገበት ምክንያት ምን እንደሆነ ሕገ-መንግሥቱ ሲዘጋጅ በአንቀጹ ላይ ከተካሄዱ ወይይቶች፤ ከፌደራል ስርዓቱ መሰረታዊ ባህሪያት እና መነሻ ምክንያቶች አንጻር የሚከተሉት ሊሆኑ እንደሚችሉ ይወሰዳል፡፡

Continue reading
  13306 Hits

The Curious Case of Construction & Business Bank

Businesses want to become big. They want their presence to be felt in every corner of the world. Investors explore different avenues to do this by injecting capital, selling equities, reinvesting their profits, opening different branch offices, acquiring other firms or merging with other entities. By the same token, corporations may also use these tactics to either dominate the market or protect their infant industry from other big entities.

All of these factors for expansion may also force Ethiopian business people to engage in changing their style of business. Nowadays, the government is trying to attract foreign investors by creating industrial parks, adding incentive packages and simplifying the service provision and bureaucratic aspects of the investment climate.

On the other hand, the government seems to engage in strengthening the capacity of its enterprises too. The focus on these enterprises may seem to either strengthen their capacity and prepare them for future challenges (or threats from other entities), or save the struggling entity through the umbrella of the successful one.

In this regard, the recent news about the amalgamation of Commercial Bank of Ethiopia (CBE) and Construction & Business Bank (CBB) can become a talking point among lawyers and economists. It can also trigger a lot of interesting debates and analyses.

Amalgamation is not a new phenomenon. It happens frequently worldwide. To give a recent example, Du Pont and Dow Chemicals, the largest US chemical companies, merged with capital of 113 billion dollars.

Continue reading
  8961 Hits

Corporate Social Responsibility as a New Way of Advertisement

 

Traditionally, corporations were responsible only to their owners; and their primary and only objective was profit maximization. Corporations’ responsibility towards the community and the environment in which they operate was overlooked. Hence, Corporations’ responsibility towards the community and the environment which is commonly known as corporate social responsibility is a recent development in the area of corporate governance.

Corporate social responsibility, often abbreviated "CSR," is a corporation's initiatives to assess and take responsibility for the company's effects on environmental and social well-being. The term generally applies to efforts that go beyond what may be required by their memorandum of association, regulators or environmental protection groups. CSR can involve incurring short-term costs that do not provide an immediate financial benefit to the company, but instead promote positive social and environmental change.

The same money and influence that enable large companies to inflict damage on people and the environment allows them to effect positive change. At its simplest, a corporation can give money to charity. Companies can also use their influence to pressure governments and other companies to treat people and resources more ethically. Companies can invest in local communities in order to offset the negative impact their operations might have. A natural resources firm that begins to operate in a poor community might build a school, offer medical services or improve irrigation and sanitation equipment. Similarly, a company might invest in research and development in sustainable technologies, even though the project might not immediately lead to increased profitability.

Today, a shift has occurred in the way people conceptualize corporate social responsibility. For decades, corporate business models have been assumed to be necessarily harmful to certain communities and resources. The intention was therefore to mitigate or reverse the damage inherent in doing business. Now many entrepreneurs consider profit and social-environmental benefit to be inextricable. 

Continue reading
  9968 Hits
Tags:

"በሕግ አግባብ"ያለአግባብ ስለመታሰር

 

ካሳ አልባ የፍትሕ ሥርዓቱ ተጎጂዎች

እንዲያው አያድርገውና በወንጀል ተጠርጥረው ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብዎ አስቸጋሪውን የወንጀል ምርመራ ተቋቁመው ካለፉ በኋላ በዓቃቤ ሕግ ተከሰው የዋስትና መብትዎን ተከልክለው ክራሞትዎ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሆነ እንበል፤ በሕግ ጥላ ሥር፡፡

የፍርድ ቤት ቀጠሮዎት በደረሰ ጊዜ እጅዎ በካቴና ተጠፍንጎ ወይም ከሌላ እስረኛ ጋር ተቆራኝቶ ጠመንጃ በወደሩ ፖሊሶች በአይነ ቁራኛ እየተጠበቁ ለወራት ወይም ለዓመታት ነጻነትዎ ተነፍጎ የፍርድ ሂደቱን ሲከታተሉና ሲሟገቱ ከባጁ በኋላ በመጨረሻ ጉዳይዎትን ይመለከት የነበረው ዳኛ የችሎቱን ጠረጴዛ በመዶሻው ግው! በማድረግ ‹‹ከተከሰሱበት ወንጀል በነፃ ተሰናብተዋል ቅንጣት ያህል ጥፋት የለብዎትም›› ብሎ ቢያሰናብትዎ ምን ይሰማዎታል???

እርግጥ ነው፣ ተሟግተው በማሸነፍዎና ንጹህነትዎን በማስመስከርዎ አልያም የእሥር ህይዎትዎ በማክተሙና ፀሐይቱን ያለ አንዳች ከልካይና ተቆጣጣሪ እንዳሻዎ ሊሞቋት በመብቃትዎ ደስታ እና እፎይታ እንደሚሰማዎ አያጠራጠርም፡፡

Continue reading
  12538 Hits

የሕግ ሙያ አገልግሎትን መቆጣጠር፣ የሕዝብ ጥቅም፣ የግለሰብ ፍላጎትና የውድድር ሕግ

በተለምዶ የሕግ ባለሙያዎች በንግዱ ዘርፍ ለሚንቀሳቀሱት ተወዳዳሪ ኃይሎች የተጋለጡ አልነበሩም፡፡ ይህ በሲቪል ሎው የሕግ ሥርዓት ተከታይ ሃገራት በአድቮኬቶችና ላቲን ኖታሪዎች እንዲሁም በኮመን ሎው የሕግ ሥርዓት ተከታይ ሃገራት በባሪስተሮች፣ ሎሊሳይቶሮች እና ኮንቬሮች መካከል ተመሳሳይ እውነታ ነበር፡፡ በእነዚህ በሁለቱ ሥርዓት የሕግ ሙያ ቁጥጥር የሚተገበረው በቀጥተኛ የመንግሥት ቁጥጥርና በላቀ ሁኔታ ደግሞ በራስ አስተዳደር (self regulation) ባለሙያዎች በተቀረፁ ሕጎች በመተዳደር ነው፡፡ ይህ የሕግ ሙያ ቁጥጥር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በእነዚህ ሥርዓቶች በፈጠረው የፀረ-ውድድር ተፅዕኖ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ እየተተቸ ይገኛል፡፡ 

Continue reading
  14167 Hits