እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል?  

 

ጥያቄው?

በዚህ ጽሁፍ መመለስ የምፈልገው ጥያቄ ቀላል ይመስላል፤ እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል የሚለውን ነው፡፡ ቀጥታ ጥያቄውን ወደ መመለሱ ከመሄዴ በፊት፤ ጥያቄው የሚመለከታቸው ሁኔታዎች ምን አይነቶቹን እንደሆነ ግልጽ ላድርግ፡፡

ያለ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ሲባል?

እንደሚታወቀው ንብረትን (የማይንቀሳቀስም ይሁን ልዩ ወይም ተራ የማይንቀሳቀስ) ለሌላ ሰው ውልን መሰረት አድርጎ ለማስተላለፍ የባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሰጥቷል ነገር ግን ፈቃዱ ሙሉ እና ነጻ አልነበረም የሚባለው የባለቤቱ ፈቃድ በስህተት ወይም በማታለል ወይም በሃይል ተግባር ምክኒያት የተሰጠና በሕጉም መሰረት ውሉ ፈራሽ ውል ሲባል ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን የገለጸው ራሱ ወይም በወኪሉ በኩል ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ሁኔታ የባለቤቱ ፈቃድ ጉድለት አለበት፤ ነገር ግን ንብረቱ ተላልፎ ሊሆን ይችላል ወይም የመብት ገደብ ተቋቁሞ ሊሆን ይችላልና እንዴት ባለቤቱ ንብረቱን ማስመለስ ገደቡን ማስነሳት ይችላል የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

ባለቤቱ በምንም አይነት መልኩ ፈቃዱን ሳይገልጽ ከሆነስ?

በሁለተኛ ደረጃ የንብረት ማስመለሱና የመብት ገደቡን የማስመለስ ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው ከመጀመሪያውኑ ባለቤቱ በምንም መልኩ ፈቃዱን ያልገለጸ ከሆነ ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሳይገልጽ እንዴት ንብረት ይተላለፋል ወይም መብት ይገደባል ለሚል ጥያቄ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሁኔታዎች መልስ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

1. አንድ ሰው ህጋዊ ባለቤት ሳይሆን ባለቤት እንደሆነ በማስመሰል ከሌላ ሰው ጋር በመዋዋል ንብረቱን ሊያስተላልፍ ወይም የመብት ገደብ ሊያቋቁም ይችላል፡፡ ንብረቱ ተራ የሚንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ይህን ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ ንበረቱ የማይንቀሳቀስ ወይም ልዩ ተንቀሳቃሽ ቢሆንም ይህን ለማደድረግ ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን ሰነዶችን ፎርጅድ ማድረግ ሊጠይቅ ወይም የሌላ አካል ትብብርን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እነዚህ ሰነዶች ይህ ሰው ባለቤት መሆኑን የሚያሳዩ ወይም ንብረቱን አስመልክቶ በባለቤቱ ስም ውል የመዋዋል ስልጣን አንዳለው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  20489 Hits

ፍርድ ቤቶች የዘነጓቸው አንገብጋቢ የተገልጋይ መብቶች

 

ፍርድ ቤቶች ሐምሌ 30 ሥራቸውን ካጠናቀቁ አንድ ሳምንት ሆናቸው፡፡ በየዓመቱ በክረምቱ አጋማሽ ተዘግቶ በመስከረም መጨረሻ የሚከፈተው ፍርድ ቤት ክረምት ጭር ይላል፡፡ የተወሰኑ የወንጀል ችሎቶችና ተረኛ ችሎቶች ካልሆኑ በቀር ፍርድ ቤቱ ከመደበኛው ሥራ ይቀዘቅዛል፡፡ አዲስ ፋይል መክፈት፣ አስቸኳይ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ (ለምሳሌ እግድ) መስጠት፣ ከበድ ያሉ የወንጀል ጉዳዮች ከመመልከት ውጭ መደበኛ ቀጠሮ አይስተናገድም፡፡ በዚህ በክረምት ወቅት ችሎቶቹ አይሠሩም ማለት እንጂ አስተዳዳሪዎቹ፣ ስለ ፍርድ ቤቶቹ የተሻለ አሠራር፣ የዳኞች አቅም የማጎልበት ሥራ፣ ስለ ሥራቸውና አገልግሎት አሰጣጣቸው የሚቀርቡ ቅሬታዎችን የማስተካከል ሥራ ላይ ይጠመዳሉ ተብሎ ይታሰባል፡፡ ፍርድ ቤቱ ልማዳዊ የፍርድ ቤት አሠራሮችን በማስቀረት፣ የዳኞችን ሥነ ምግባር በመቆጣጠር እንዲሁም ለተገልጋዮች ምቹ የሚሆንበትን ሥራ የሚያስብበት ወቅት በመሆኑ፣ በዚህ ጽሑፍ በፍርድ ቤቶች የተዘነጉ ግን ተገልጋዮችን እየጎዱ ባለ ልማዶችና አሠራሮች ላይ የተወሰነ ምልከታ ለማድረግ እንሞክር፡፡

የመፀዳጃ ቤቱ ነገር

መፀዳጃና ፍርድ ቤት ምን አገናኛቸው እንዳልይባል ከገጠመኝ ልጅምር፡፡ በልደታ ፍርድ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተገልጋዮች መግቢያ በቀኝ በኩል ባሉት የድሮ ሕንፃዎች ጀርባ ሰዎች ተጣድፈው ሲገቡ ቀልቤን ሳቡኝ፡፡ ገንዘብ ቤት ወይም ኮፒ ቤት የሚሄዱ ቢመስልም ፍጥነታቸው የሚያሯሩጥ ሰው ያለ ነው የሚመስለው፡፡ ቀረብ ብዬ አንድ ወዳጄን ‹‹ሰዎቹ የት እየሄዱ ነው?›› ብዬ ስጠይቀው፣ ‹‹የተፈጥሮ ግዴታ ወጥሯቸው›› በማለት ሰዎቹ የሽንት ወረፋ ለመያዝ እንደሚቻኮሉ ነገረኝ፡፡ ከፍርድ ቤት ቅጥር ውጭም ባለጉዳዮችና ጠበቆች ሳይቀሩ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት ካለው ኒያላ ሆቴል ጀርባ ለሽንት ማዘውተራቸው የተለመደ ነው፡፡ ድንገት ተራቸው ደርሶ ከተጠሩ ‹‹ኒያላ ሆቴል ለሽንት ሄደው ነው›› ቢባል የሚረዳ ይኖር ይሆን? ፍርድ ቤቶቻችን በጤና መሥፈርት አንፃር ቢገመገሙ ኖሮ አሁን ካሉበት ደረጃ የባሱኑ ዝቅ ሊሉ እንደሚችሉ መገመት ይቻላል፡፡ በርካታ ባለጉዳይ የሚስተናገድበት ፍርድ ቤት ለባለጉዳዮች፣ ለጠበቆች፣ ለነገረ ፈጆች የሚሆኑ መታጠቢያ ቤቶችና የመፀዳጃ ቤቶች የላቸውም፡፡ አዲስ በተሠራው የልደታው ፍርድ ቤት ሕንፃ ሳይቀር ሽንት ቤት ባለመኖሩ ጠበቆችና ባለጉዳዮች ከፍርድ ቤት ውጭ በየካፌውና ሬስቶራንቱ ሲዞሩ ይውላሉ፡፡ በዚህ ዘመን ዘመናዊ ሕንፃዎች አይደሉም የገጠሩ ማኅበረሰብ እንኳን የመፀዳጃ ቤት እንዲያዘጋጅ በሚመከርበት ወቅት፣ ትናንሽ ግሮሰሪዎችና ካፌዎች እንኳን መፀዳጃ ቤት ለደንበኞቻቸው በሚያቀርቡበት ጊዜ ፍርድ ቤቶች ረዥም ሰዓት ለሚያስቆሙዋቸው ባለጉዳዮቻቸው የተፈጥሮ ግዴታቸውን የሚወጡበት ቦታ አለማዘጋጀታቸው ደንበኛ ተኮር እንዳይሆኑ አድርጓቸዋል፡፡ በሰኔ ወር በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በተዘጋጀ ጉባዔና የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር በሐምሌ አጋማሽ በፍትሕ ሚኒስቴር ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጠበቆች ‹‹ኧረ የመፀዳጃ ቤቱን ነገር አደራ!!›› የሚል መልዕክት ለፍርድ ቤቶቹ አመራሮች አሰምተዋል፡፡ አንዳንድ ጠበቆች ከልምዳቸው እንደሚናገሩት ከፍተኛ ታዋቂነት ያላቸውና የውጭ ዜጎች ሳይቀሩ የመፀዳጃ ቤት ጥያቄ ባቀረቡ ጊዜ አለማስተናገዳቸው የፍርድ ቤቱን ገጽታ እንደሚያጎድፈው ይናገራሉ፡፡ ሕፃናትና ነፍሰ ጡሮች፣ አረጋውያንና የታመሙ ሰዎች በሚገኙበት ፍርድ ቤት ለአስቸጋሪ ሁኔታ የሚጠቅም መታጠቢያ ቤትና መፀዳጃ ቤት አለመኖሩ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ የድሮዎቹ ፍርድ ቤት ለዳኞች መፀዳጃ ቤቶችን ሲያዘጋጁ ባለጉዳዮቹንም አይዘነጉም ነበር፡፡ ለዚህ ነው በአዲስ ባልተተኩት የድሮ ሕንፃዎች ንጽህናቸው አጠያያቂ ቢሆንም፣ ለባለጉዳዮች ሽንት ቤቶች አዘጋጅተው የምናስተውለው፡፡ የሽንት ቤት ነገር የፍርድ ቤቶች አስተዳዳሪ አካል የክረምት የቤት ሥራ ይሆናል ብለን ተስፋ እናድርግ፤ ካልሆነ ጤና ጥበቃ የሽንት ቤቱን ጥያቄ በይግባኝ እንዳይመለከተው፡፡

ጊዜ ዋጋ የሚያገኘው መቼ ነው?

Continue reading
  12955 Hits
Tags:

በቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት ያለመቅረብ ውጤቶች

 

ተከራካሪ ወገኖች እራሳቸው ወይም በተወካያቸው አማካይነት ፍርድ ቤት በሚወስነው በማንኛውም ቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከሳሽ አንድ ጊዜ ጉዳዩን ይዞ ከቀረበ በኋላ ተከታትሎ ከዳር ማድረስ መቻል ያለበት ሲሆን ተከሳሽም በእያንዳንዱ ቀጠሮ እየቀረበ የቀረበበትን ክስ በአግባቡ መከላከል መቻል አለበት፡፡ክስ ያቀረበ ሰው በሁሉም ቀጠሮዎች ንዲገኝ የሚጠበቅበት ቢሆንም በተያዘው ቀጠሮ ባለመገኘቱ ምክንያት ያቀረበውን ክስ መዝጋት ጨምሮ እንደ ቀጠሮው ምክንያት ሌሎች ትእዛዞች ሊሰጡ ይችላሉ፡፡ ክሱ ሊዘጋ የሚችለው ሕጉ ለይቶና ዘርዝሮ ባስቀመጣቸው ምክንያቶችና ጋጣሚዎች ብቻ ነው፡፡ የፍርድቤት ክርክር በከሳሽ እና ተከሳሽ ይሁንታ ላይ ተመስርቶ በፈለጉ ቀን የሚቀርቡበት ደስ ካላላቸው ደግሞ የማይቀርቡበት ሂደት አይደለም፡፡

ንድን ጉዳይ ለማየት የተሰየመ /ቤት የተለያዩ ክንዋኔዎችን ለመፈፀም በርካታ ቀጠሮዎች ንደሚሰጥ የታወቀ ነው፡፡ በሙግት ሂደት ፍርድ ቤት የተለያዩ ጉዳዮች መከናወናቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ቀጠሮዎችን ይሰጣል ይላል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድቤት ሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥር 14184፡፡ ንድን ጉዳይ ይቶ ውሣኔ ለመወሰን በርካታ ቀጠሮዎችን ፍርድ ቤት ንደሚሰጥ የሚታወቅ ሲሆን ከነዚህ በርካታ ቀጠሮዎች መካከል ንዱ ወይም በሌላኛው ወይም በሁለቱም ለመቅረብ ምክንያት ፍርድ ቤት የተለያዩ ትዕዛዞችን እንደሚሰጥ አትቶታል መዝገቡ፡፡ የቀጠሮ ለመከበር ቀጠሮ ከተሰጠበት ምክንያት ተነጥሎ የሚታይ ባለመሆኑ የቀጠሮውን ምክንያት ከግምት በማስገባት የሚሰጠውም ትእዛዝ የተለያየ ነው፡፡

አንድ የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ተከራካሪ ወገኖች ክሱ በማንኛውም ደረጃ ላይ ባለበት ጊዜ መቅረብ ባይችሉ ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ድንጋጌዎች ነዚህን ሁኔታዎች በቅጡ ለመገንዘብ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጋችን የከሣሽ ና/ወይም የተከሣሽ ለመቅረብ (non appearance of parties) ስመልክቶ ያስቀመጠውን ሥርዓት ጠቃላይ የሙግት ሂደት ጋር ገናዝቦ መመልከቱ ጠቃሚ ነው ይላል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳዩን በተመለከቱ ፍርዶቹ፡፡

በዚህ ጽሑፍም ፍርድ ቤት ከሚሰጣቸው የተለያዩ ቀጠሮዎች እና ውጤታቸው ጋር በተያዘ የፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉን ድንጋጌዎች እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

Continue reading
  22241 Hits

Justification of Excise Tax in General

 

Excise taxes are an example of what have been traditionally called indirect taxes: taxes that are imposed on a transaction rather than directly on a person or corporation. Excise taxes are narrow-based taxes, as compared with broad-based taxes on consumption such as a general sales tax, a value-added tax, or an expenditure tax. Excise taxes can be collected at various stages, including the point of production, the wholesale level, or the retail level. They are also known as selective sales taxes or differential commodity taxes.

Excise taxes are levied on either a unit or ad valorem basis. For unit (also known as specific) excises, the tax is denominated in terms of money per physical unit produced or sold. Examples include the federal government taxes of 18.4 cents per gallon of gasoline, $13.50 per gallon of distilled spirits, and $3.10 per domestic flight segment for passenger airline travel. Ad valorem excises are based on a percentage of the value of the product or service sold. The 7.5 percent federal tax on the cost of domestic airline passenger tickets and the 3 percent tax on the cost of telephone services are examples of ad valorem taxes.

Broader-based taxes, such as the income and general sales taxes, are difficult to administer when most of the economic activity takes place outside a structured market setting. Excise taxes are sometimes used as a means of implementing an ability-to-pay approach to taxation. So-called luxury taxes are an example of this approach.1 The United States currently levies an excise tax on expensive passenger vehicles. This tax is set at 10 percent of the value in excess of a floor amount of $30,000. The tax on high-value automobiles has also been explained as a means of making foreign imports (which comprise a large percentage of such vehicles) more expensive than domestic Automobiles. By taxing items consumed disproportionately by higher-income individuals, excise taxes can achieve an element of progressivity. There are questions, however, concerning horizontal equity because not all people at the same income level have similar expenditure patterns for luxury items.  Excises are also levied on goods or services that are considered harmful or undesirable, in an Attempt to discourage consumption. Taxes based on this rationale are labeled sumptuary excises.  Examples include taxes on alcoholic beverages, tobacco products, and wagering. Because many of the goods and services taxed by sumptuary excises have relatively inelastic demands, these taxes May have only a limited impact on curtailing consumption. This presents an added benefit, however, for the government in that it provides a relatively stable source of tax revenue. Sumptuary Taxes are often popular politically because many citizens do not engage in the taxed activities, whereas purchasers of the taxed items do so voluntarily. Such taxes may have negative consequences from the standpoint of vertical equity because sumptuary excises are often highly regressive. Excises may also be imposed as a technique for dealing with negative externalities. This is related in some ways to the sumptuary excises. Taxes on “gas guzzling” automobiles and gasoline can be explained as a kind of Pigouvian (corrective) tax to reduce the divergence of the private and social costs relating to pollution or congestion. Such taxes are usually an imperfect technique for internalizing externalities, because an efficient Pigouvian tax should be related to the marginal damage caused by an activity, which is not necessarily proportional to the level of consumption.

Finally, excise taxes may be employed as a means of implementing a benefits-received approach to taxation. Gasoline taxes are an example. Gasoline usage is closely related to highway travel, thereby providing a link between taxes paid and benefits received from roadways. This link is further strengthened by earmarking where the revenues collected from an excise tax are designated for use in providing government services related to the activity. Examples include the earmarking of motor fuel taxes for highways and taxes on airline tickets for air traffic control and facilities expansion.  

Continue reading
  19496 Hits

Victim Oriented Measures under Ethiopian Anti-Human trafficking Law

“Violations of human rights are both a cause and a consequence of trafficking in persons.”

                                      UN human rights office of the High Commissioner, fact sheet 36

 Introduction

Traditionally, People in Ethiopia feel that living abroad is life changing and take it as a privilege. In country sides there is customarily mainstreamed saying that እልፍ ቢሉ፤እልፍ ይገኛል/ Eliff bilu elf yignagal” meaning that if somebody changes a living place she or he will get a decent life counted in thousands. That’s why many peoples in Ethiopia left their home and searching jobs abroad via illegal means and fall in the hands of satanic and barbaric traffickers in turn witnessed dozens of sufferings.

To begin with, trafficking in persons, especially women and children, is increasingly becoming an issue of global concern. It is evident that the fons et origo of human trafficking problem at the international arena at least dates back to the Paris conference on trafficking in women held in 1895.

Continue reading
  11857 Hits

ጥንቃቄ የሚፈልገው ዳኞችን የመሾም ሥርዓት

በማንኛውም አገር የመንግሥት አስተዳደር ከሕግ አውጪውና ከሕግ አስፈጻሚው እኩል የዳኝነት አካሉ አደረጃጀት፣ አወቃቀርና ጥንካሬ የሥርዓቱን ዴሞክራሲያዊነት ይወስናል፡፡ የዳኝነት አካሉ ገለልተኛና ነፃ ባልሆነ መጠን የሥርዓቱ ዴሞክራሲያዊነት ዋጋ ያጣል፡፡ የዳኝነት አካሉ መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ መርሆችን ለማስፈጸም፣ የዜጎች የሰብዓዊ መብቶች እንዲጠበቁና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ገለልተኛ፣ ግልጽ አሠራርን የሚከተልና ጠንካራ እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ 1987 .. የወጣው ሕገ መንግሥታችን በአንቀጽ 78 እና 79 እነዚህ መሠረታዊ የዳኝነት አካሉ መገለጫዎችን ደንግጓል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ መንግሥቱ ከወጣ 25 ዓመታት በኋላም የዳኝነት አካሉ የአሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት አመርቂ እንዳልሆነ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይስማማሉ፡፡ ለዚህ ነው የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2015 . በሕዝብ ታማኝነት ያለው የዳኝነት አካል ለመሆን ራዕይ ይዞ የሚንቀሳቀሰው፡፡ 15 ቀናት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፀደቀው የዳኝነት ሹመት ጋር በተያያዘ በሕግ ባለሙያዎች በየዐውዱ የሚደረገው ክርክር የዚህ አንዱ መገለጫ ነው፡፡ ኃይለ ገብርኤል መሐሪ የተባሉ ጸሐፊ ሰኔ 26 ቀን 2008 .. በሪፖርተር ጋዜጣ የአስተያየት አምድ ‹‹ግልጽነት የጎደለው የዳኞች ምልመላ›› በሚል በጻፉት ጽሑፍ የተሾሙት ዳኞች ምልመላ በአጭር ጊዜ የተፈጸመ፣ በቂ ፈተናና ግምገማ ያልተደረገበት፣ የሕዝብ አስተያየት በአግባቡ ያልተወሰደበትና ግልጽነት የጎደለው እንደነበር ይገልጻሉ፡፡ ጸሐፊውን ጨምሮ በፍርድ ቤቶች አካባቢ የሚታዩ ጠበቆችም የዳኞቹ አመላመልና ሹመት ጋር በተያያዘ ሊታዩ የሚገቡ ነጥቦች እንዳሉ ያምናሉ፡፡

የዳኞች አመላመልና አሿሿም የዳኝነት አካሉን ነፃነት ከሚያረጋግጡ ቅድመ ሁኔታዎች ዋናው ነው፡፡ ዳኞችም ከማንኛውም ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ተፅዕኖ ነፃ በመሆን ፍትሕ እንዲሰፍን የሚሠሩት ምልመላውና አሿሿሙ ግልጽና ተጠያቂነት ሲኖረው ነው፡፡ የዳኞች አሿሿም የዳኝነት አካሉን ነፃነት ከሚያስገኙ የገለልተኝነት፣ የብቃት፣ የሃቀኝነትና የነፃነት እሴቶች ጋር እጅጉን ይቆራኛል፡፡ የዳኝነት አካሉ በኅብረተሰብ ውስጥ ተገቢውን ቦታ እንዲያገኝ በግልጽነት የዳኞችን የመሾም ሥርዓት ሊያከናውን ይገባል፡፡ ይህ የሚሳካው ደግሞ የዳኞች የአመራረጥና የአሿሿም ዘዴ፣ የሚመረጡ ዳኞች ዕውቀትና ልምድ በጥንቃቄና በኃላፊነት ሲከናወን ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ከዳኝነት አሿሿም ጋር በተያያዘ ጥንቃቄ የሚፈልጉ አንዳንድ ነጥቦችን ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

የዳኝነት አሿሿም ዘዴዎች

የዳኝነት አሿሿም እንደ አገሮቹ የፖለቲካ ባህልና ማኅበራዊ እሴት ይለያያል፡፡ አንድ ወጥ የአሿሿም ሥርዓት የለም፡፡ ማንኛውንም የአሿሿም ሥርዓት የሚከተል አንድ አገር የዳኝነት አካሉ ነፃ እንዲሆን የአሿሿም ሒደቱ ግልጽና ኅብረተሰቡን ያሳተፈ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ግልጽነትና የሕዝብ ተሳትፎ በአሿሿም ካለ ጥራትና ብቃት ያላቸው የሕግ ባለሙያዎች ዳኛ ይሆናሉ፡፡ ኅብረተሰቡ በዳኝነት አካሉ ላይ ያለው መተማመን ይጨምራል፡፡

በተለያዩ አገሮች ተፈጻሚ የሚሆኑ የዳኝነት አሿሿም በደምሳሳው በሁለት ሊከፈል ይችላል፡፡ አንዱ በምርጫ የሚከናወን ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በመሾም ሥርዓት የሚከናወን ነው፡፡

Continue reading
  8720 Hits

የኮንስትራክሽን መብቶች (Claims) ምንነት እና የሚስተዋሉ ችግሮች

 

እንደ መነሻ

ማንኛውም ሰው በማህበራዊ ኑሮ ውስጥ በሚገጥመው መስተጋብር የተለያዩ ጥያቄዎች ወይም መብቶች (Claims) ሊኖረው ይችላል፡፡ ከዚህ ንድፈ ሃሳብ በመነሳት ታዲያ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውም በርካታ የመብት ጥያቄዎች መነሳታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው! እንደሚታወቀው የግንባታ ዘርፍ ብዙ ባለድርሻ አካላትን ማሳተፋ ብቻ ሳይሆን የሚገርመው በተለያየ ሙያ ያሉ ሰዎች መሳተፋቸውም ጭምር ነው፡፡ ይህም በመሆኑም በርካታ የመብት ጥያቄዎች መነሳታቸው የግድ ነው፡፡ ከዚህ ብሂል በመነሳት አንዳንዶች ከውል በመነጨ ጉዳይ የውል የመብት ጥያቄ ሲያነሱ ሌሎች ደግሞ ሕጉ አስቀድሞ ባስቀመጠው ቅድመ ሁኔታ መሠረት ውል ሳይኖር አላፊነት በመኖሩ ምክንያት መብታቸውን ከውል ውጭ ሲጠይቁ ይስታዋላል፡፡

ምናልባት በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ ለሚነሱ አለመግባባቶች እና ቁርሾዎች እንደ ምክንያትነት የሚነሣው የመብቶች ጥያቄ ጉዳይ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ቅድሚያውንም የሚወስዱት በተለይም ከሥራ ርክክብ መዘግይት እንዲሁም ከውል መለወጥ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በሃገራችንም ምንም እንኳን ልማዱ በዓለም አቀፍ ሥራ ተቋራጮች በርከት ቢልም ቅሉ፤ የሃገር ውስጥ ሥራ ተቋራጮችም ቢሆን አሁን አሁን የተለያዩ የኮንስትራክሽን የመብት ጥያቄዎች ሲያስተጋቡ ይስተዋላል፡፡

Continue reading
  17181 Hits

የግል አቤቱታ የማቅረብ መብት በጠቅላላው

 

መግቢያ

የሥነ-ሥርዓት ሕግ ሰዎች መሠረታዊ የሆኑ የፍትሕ አቤቱታዎች ሲቀርቡ የሚመሩበትን እና መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በሚመለከታቸው የፍትሕ አካላት የሚወስኑበትንና ተፈፃሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን ሥርዓት የሚያሳይ ጽንሰ ሀሳብ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕግ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በምንና እንዴት ባለ አኳኋን ወደ ተግባር ሊፈፀሙ እንደሚችሉ የሚዘረዝር የሕግ ክፍል ነው። የእነዚህን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች ይዘትና አይነት ተንትኖ የሚያቀረበው የሕግ ክፍል መሠረታዊ ሕግ (Substantive Law) ተብሎ የሚጠራ ነው። መሠረታዊ ሕግ የሰው ልጆችን መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች በግልፅ የሚደነግግ በመሆኑ ጠቀሚታው ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ይሁን እንጅ እንዚህ ዝርዝር መብቶችና ግዴታዎች በተግባር ተፈፃሚ እንዲሆኑ ካልተደረገ የመኖራቸው ጉዳይ ትርጉም የለሽ ይሆናል ማለት ነው። እነዚህ መደበኛና ልዩ መብቶች ጥቅሞችና ግዴታዎች እንዲፈፀሙ የማድረጉ ሐላፊነት የሥነ-ሥርዓት ሕግ ቢሆንም ውጤታማ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከሌለ ግን መብቶችንና ግዴታዎችን የማስፈፀሙ ዓላማ እረብ የለሽ ይሆናል። ለዚህም ነው የሥነ-ሥርዓት ሕግ ከመሠረታዊው ሕግ ባላነሰ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው የሚባለው።

በግልፅ መረዳት እንደሚቻለው ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ የሥነ-ሥርዓት ሕግ ያለው አስተዋፆ በጣም ከፍተኛ ነው። የሥነ-ሥርዓት ሕጉን ዓላማና መንፈስ መከተል ተከትሎም ተፈፃሚ ማድረግ በራሱ ፍትሕን ማረጋገጥ ነው የሚሆነው። የፍትሕ ጉዳይ ‹‹የትም ፍጪው ዱቂቱን አምጭው›› የምንለው ነገር ሣይሆን ከመነሻው እስከ መዳረሻው ያለውን ሂደትና ሥርዓት በመከተልና በመተግበር የሚገኝ ፍርድ ስለሆነ የሥነ-ሥርዓት ሕጎችን እውቀት ማሳደግ ለትክክለኛ ፍትሕ አሰጣጥ ቁልፍ ሚና አለው።

የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥዓት የወንጀል ጉዳዩች የሚመሩበት የሚከሰሱበት የሚዳኙበት የሚቀጡበትን  ሥርዓቶች  የሚገዙ ደንቦች  ናቸው።  ይህም  ትንሽ  የማይባሉትን የመሠረታዊ ወይም የዋና መብቶች ደረጃ አግኝተው በሕገ-መንግስት እና  በዓለም-አቀፍ  ኮቬናንቶች ጥበቃና  አውቅና  ያገኙትን የተከሣሾች የሥነ-ሥርዓት መብቶች ያካትታል። 

Continue reading
  17354 Hits

Status and Application of Juvenile Related International Frameworks in Ethiopia

The applicability of international frameworks, in general, depends initially on the status a given country gives to international instruments in its legal system. Its commitment begins with the clear statement it makes regarding the status and application of those ratified instruments. This is why usually States determine in their domestic legislations status related issues such as incorporation, hierarchy, implementation mechanisms, implementing institutions, etc of international instruments. This topic briefly discusses the status and applicability of juvenile justice related international instruments, particularly the ACRWC and the CRC, in Ethiopia.

International law does not recognize a specific mode of incorporation of international instruments leaving the room for States to choose their own way of incorporation. Because of this, modes of incorporation differs from one country to the other traditionally falling either in monism (mostly followed by civil law countries), where international law and domestic law are part of the same legal order by virtue of declaration made to that effect usually in the Constitution, and dualism (followed by common law countries), where international law is separate and not directly applicable in the domestic order unless incorporating/enabling legislation is passed to that effect.

Other modes of incorporation are also recognized by other scholars such as Cassese. One is, Automatic Standing Incorporation, whereby states declaring present or future international rules to apply without the need to pass statutes. This mode of incorporation resembles with the monist mode. The second, Legislative ad hoc incorporation requires the legislator to pass specific enabling statute regarding the treaty. The statute, commonly known as ratifying legislation usually include three or four provisions presenting ‘short title’, ‘ratification clause’, ‘scope of application’, and ‘effective date. The third mode of incorporation is called statutory ad hoc incorporation, which requires the legislature to convert every detail of treaty provisions in to national legislation.

The mode of incorporation in Ethiopia appears confusing seemingly utilizing all above discussed modes. Article 9(4) of the FDRE Constitution recognizes the monist mode or automatic standing incorporation mode by declaring every ratified treaty to form ‘an integral part of the law of the land’. Therefore, the Constitution enabled international treaties to apply directly as part of the laws of the land up on ratification.

The dualist or legislative ad hoc, or statutory ad hoc modes of incorporation also seem to exist in Ethiopia. The Federal Negarit Gazeta Establishment Proclamation (the Proclamation) requires publication of every law either duly enacted domestically or ratified to have legal effect. Based on this the practice developed incorporation of treaties in the form of statutory ad hoc mode

Continue reading
  9384 Hits

አትሌቶች፣ ዶፒንግና ግልግል (arbitration)

 

ማሪዮን ጆንስ፣ ማሪያ ሻራፖቫ፣ ክላውዲያ ፔከንስታይ እና ላንስ አርምስትሮንግን የሚያመሳስላቸው አንዱ በስፖርቱ ዓለም ገናና ስም የነበራቸው መሆኑ ነው፡፡ ማሪዮን ጆንስ የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ናት፡፡ አርምስትሮንግ ደግሞ በብስክሌት ግልቢያ የሚያህለው አልነበረም፡፡

ማሪዮን ጆንስ አጭሩን ርቀት በሚያስገርም ፍጥነት ታጠናቅቅ ነበር፡፡ የአሸናፊነት ምልክትም ሆና ለብዙ ዘመን ቆይታለች፡፡ አርምስትሮንግም እንዲሁ፡፡ ከችሎታውና ብቃቱ የተነሳ ስፖንሰሩ ለመሆን ያልተሯሯጠ ኩባንያ አልነበረም፡፡

በአንደኝነት ያላጠናቀቀበት ውድድርም ማግኘት አዳጋች ነበር፡፡ ‹‹ቱር ደ ፍራንስ›› በመባል የሚጠራውን የብስክሌት ውድድር ብዙ ጊዜ አሸንፏል፡፡ በብር ላይ ብር፣ በክብር ላይ ክብር ደርቧል፡፡ እሱ ካለው ዝና የተነሳ የካንሰር ታማሚዎችን የሚደግፈው ‹‹ሊቭ ስትሮንግ›› የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅቱም በርካታ ሚሊዮን ዶላሮች ይጎርፉለት ነበር፡፡ ከእርሱ ጋር መሥራት ‹‹ኩራታችን›› ነው ያሉ ድርጅቶችም ብዙ ነበሩ፡፡ የ44 ዓመቷ ክላውዲያ ፔከንስታይ የበረዶ ላይ መንሸራተት ስፖርተኛ ናት፡፡ ገድሏ እንደሚተርከው ባደረገቻቸው ዓለም ዓቀፍ ውድድሮች 60 ሜዳሊያዎችን አሸንፋለች፡፡

ፍጻሜው

Continue reading
  12316 Hits