የተሸከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሕግ በኢትዮጵያ

በሀገራችን ኢትዮጵያ የተሸከርካሪ አደጋ በእጅጉን እየበዛ እና ከፍተኛ የሆነ የሞትና የንብረት ጉዳት እያስከተለ ይገኛል፡፡ የበርካቶች ህይወት አጥፍቷል፣ አካል አጉድሏል እንዲሁም ንብረት አውድሟል። ሁልግዜ በየማለዳው በራዲዮ የምንሰማቸው የትራፊክ ዘገባዎችም እጅግ ዘግናኝ እና ሁላችንንም የሚያስደነግጥ፣ የህሊና እረፍት የሚነሳ እና ወቶ የመግባት ዋስትናችንን ጥርጣሬ ውስጥ የሚከት ወደመሆን ደርሶል፡፡ ችግሩ እጅግ አሳሳቢ እና አስከፊ የሚያደርገው ደግሞ ጉዳት አደራሾቹ በአደጋው ተጋላጭ ለሆኑት ግለሰቦች እርዳታ ከመስጠት ወይም እርዳታ እንዲያገኙ እና ህይወታቸው እዲተርፍ ከማድረግ ይልቅ ጉዳቱን አድርሰው የሚሰወሩ መሆናቸው ነው፡፡

  26431 Hits