ስለዊዝሆልድንግ ታክስ

መግቢያ

በታክስ ሥርዓት ላይ ጥናታቸውን የሰሩ ባለሙያወች “the tax system must be dynamic with in the dynamic world ” - ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ውስጥ የታክስ ሥርዓቱ ተለዋዋጭ ካልሆነና ዓለም በፈጠረው ቴክኖሎጅ የሚደረገውን የታክስ ስወራ ተግባር መከላከል፣ መቆጣጠር እንድሁም ድርጊቱ ተፈፅሞ ከተገኘ ሊቀጣ የሚችል ሥርዓት ካልዘረጋ የአንድ ሀገር ህልውና አደጋ ላይ ይወድቃል ይላሉ፡፡ እኔም ይህንን ሀሳብ ከሚጋሩ ባለሙያዎች አንዱ ነኝ፡፡ በመሆኑም አንድት ጠንካራ ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት ዘመናዊ ዓለምን ያማከለ ዘመናዊ የታክስ ሥርዓት መዘርጋት ስፈልጋል፡፡ ይህ ተግባር ደግሞ ገቢን በግልፅነትና ተጠያቂነት፣ በፍትሃዊነትና እኩልነት እንድሁም በዘላቂነት መሰብሰብና ማሳደግ የሚችል ሕግ ከማውጣት ይጀምራል፡፡ ሕግ ማውጣት ብቻ ሳይሆን የወጣውን ሕግ ማስፈፀም የሚችል ተቋም እና ሠራተኛ መገንባት ያስፈልጋል፡፡ ተቋሙ እና እያንዳንዱ ሠራተኛ ደግሞ በየደረጃው የወጡ ሕጎችን ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የማሳወቅ ሞራላዊ ግደታ አለበት፡፡ ሆኖም ከቅርብ ጊዜ ወድህ በግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና በፍ/ቤቶች ቅሬታ እያስነሳያለው የግብር ዓይነት ተቀንሶ የሚያዝ ታክስ/ዊዝሆልድንግ ታክስ ሲሆን ለዚህ ጽሑፍ ዓላማ ከእነዚህ ታክሶች አንዱ የሆነውን እና በንግድ ማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና በተግባር የአፈፃፀም ችግር የሚታይበትን በገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/08 አንቀፅ 92 ላይ የተቀመጠውን በሀገር ውስጥ ከሚፈፀሙ ክፍያወች ላይ ተቀንሶ የሚያዝ ግብርን በዝርዝር ለመዳሰስ እምክራለሁ፡፡ ወደ ጉዳዩ ከመግባቴ በፊት ግን ዊዝሆልድንግ ታክስ ምን ማለት እንደሆነ ትርጉም ሰጥቼ ማለፍ እፈልጋለሁ፡፡

  30204 Hits

የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ የተሰጠው ሰው እና በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ንዑስ-ሥራ ተቋራጭ የግብር ግዴታ

መግቢያ

ማንኛውም ገቢ የሚያገኝ ሰው በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 እና በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 መሰረት ግብር የመክፈል ኃላፊነት አለበት፡፡[1] በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት፤ በኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው የትርፍ ድርሻ፣ የንዑስ ሥራ ተቋራጭ፣ የወለድ፣ የሮያሊቲ፣ የሥራ አመራር፣ የቴክኒካል፣ የመድን አረቦን፣ ወደ ውጭ አገር የሚላክ ትርፍ፣ እንዲሁም የሌሎች ገቢዎች ክፍያ ሲፈጽሙ ከጠቅላላ ክፍያው ላይ በግብር ሕጉ መጣኔ መሰረት ግብር ቀንሰው መያዝ እንዳለባቸው ተደንግጓል፡፡[2] በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ፣ ከትርፍ ድርሻ ወይም ካልተከፋፈለ ትርፍ፣ ከወለድ፣ ከሮያሊቲ፣ እና ከሌላ በአገር ውስጥ ከሚፈጸም ክፍያ ላይ በግብር ሕጉ መጣኔ መሰረት ግብር ቀንሰው መያዝ አለባቸው፡፡[3]

  6116 Hits

A Brief Note on Ethiopia’s Tax Privileges to ease the Impact of Covid-19

The outbreak of the COVID-19 pandemic has brought overall economic, political and social crisis in most parts of the world, including Ethiopia. Although there are criticisms on their effectiveness, the government of Ethiopia has been taking measures to ease the economic impact of COVID-19 on the business entities operating in the country. Earlier in April, a protocol was issued by the Ministry of Labor and Social Affairs cited as the COVID-19 Workplace Response Protocol, which regulates the relationship between employees and employees during the COVID-19 pandemic. This protocol was a subject of criticisms due to its silence on the obligation and role of the government in sharing the burdens of employers.  

  8273 Hits