ስለ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች መልስ የሚሹ ጉዳዮች

በተደራጀ እና በብሔራዊ ሕግ ዕውቅና አይሰጣቸው እንጂ በኢትዮጵያ የሸሪኣ ሕግን መሠረት በማድረግ ውሳኔ መስጠት የቅርብ ታሪክ አይደለም፡፡ በታወቀ ሁኔታ እና በመንግሥት ድጋፍ የሸሪኣ ፍርድ ቤቶች የተቋቋሙት ግን በ1934 ዓ.ም. ነው፡፡ ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ሕጉ ከሁለት ዓመት በኋላ ተሻሻለ፡፡ ቀጥሎም አገሪቱ በፌደራል ሥርዓት መተዳዳር ከጀመረች በኋላ በ1992 ዓ.ም. እንደ አዲስ የፌደራል ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች ተቋቋሙ፡፡ በፌደራል ብቻ ሳይወሰኑ በክልሎቹም እንዲሁ ተቋቋሙ፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋና መሠረቱ አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገ መንግሥት ነው፡፡ በአንዳንድ ክልሎች፣ ከመደበኛው ፍርድ ቤት ጎን ለጎን በችሎትነት ሲቋቋሙ በፌደራል ደረጃ ግን ራሳቸውን ችለው የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛ እና ጠቅላይ ሸሪኣ ፍርድ ቤቶች በመባል ተቋቁመዋል፡፡

  16402 Hits