በክልል የተገደበው የመዘዋወር ነፃነት

1. የመዘዋወር ነፃነት አለም አቀፋዊ አንድምታው

የሰው ልጅ ሰው ሆኖ በመፈጠሩ ከሚያገኛቸው አያሌ የተፈጥሮ መብቶች ውስጥ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ የሰው ልጆችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነት ከሐይማኖት፤ ከባህል እና ከሌሎች የተፈጥሮ ህግጋት ጀምርን ስንመለከተው ፅኑ መሰረት ያለው ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በአለማችን ታሪክ ይህ ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት በአንዳንድ የታሪክ አጋጣሚዎች ላይ ተገድቦ የነበረ ቢሆንም በአብዛኛው ግን ሰዎች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብታቸው ሲከበር ቆይቷል፡፡ ይሄንን ተፈጥሮአዊ መብት በመጠቀም የተለያዩ የአውሮፓ ሰዎች አዲስ ግኝትን፤ የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሀገሮች ደግሞ ንግድን በማጧጧፍ ለሀገራቸው እና ለአህጉራቸው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አበርክተዋል፡፡ ይህንን ጥቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደ ማግና ካርታ (Magna Carta) አይነት ጥንታዊ ሰነዶች ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብትን አውጀዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በታላቋ ሮም የነገሱ አብዛኛው ነገስታት ከቦታ ቦታ የመዘዋወር ነፃነትን ሲያከብሩ መቆየታቸውን የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

  11552 Hits