Examining Workers Rights, Occupational Safety Measures and Benefits amid Covid-19 Under Ethiopian Labour Law

 

Introduction

The outbreak of CODIV-19 has caused employment crisis worldwide as the virus is claiming thousands of lives and sickening a millions. The virus is causing global economic, social, health, and economic disruptions. The International Labour Organization has an estimate that up to 25 million jobs could be lost worldwide. In addition to the possible unemployment crisis, the safety and health of workers are at risk. Following the declaration of the virus as a Public Emergence of  International Concern  and pandemic by World Health Organization, countries are taking different measures including partial or full lockdown. Ethiopia is not an exception to this crisis, and the same measures are being taken by the government.

During crisis, Labor Law responds with safety and health measures, benefits and rights for workers. However, CODIV-19 pandemic has brought new challenges to some static provisions of the labor law, including the ILO protocols and guidelines. The Ethiopian labor proclamation has also suffered from some lacuna to combat the CODIV-19 pandemic having static provisions in normal cases. Hence, the discussion as to new challenges posed by the new pandemic to the Ethiopian labor law, the adequacy of existing legal responses available, the safety and health measures needs to be taken, and the workers' rights and benefits related with this outbreak is imperative and timely.

The Issue

Continue reading
  6170 Hits

የኮቪድ 19 ወረርሸኝና የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ

 

በዓለማችን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን እየተስፋፋ በመምጣቱ ከአሜሪካ እስከ አፍሪካ፣ ከአውሮፓ እስከ እሲያ ከአውስትራሊያ እስከ ደቡብ አሜሪካ መንግስታት፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ግዙፍ የንግድ ድርጅቶች አነስተኞቹን ጨምሮ እንቅስቃሴያቸው እየተናጋ፤ ህልውናቸው ፈተና ውስጥ እየገባ ነው፡፡ ይህ ወረርሽን ማብቂያው እና መወገጃው በግልጽ ያልታወቀ እና ሊተነበይም ያልቻለ በመሆኑ በተለይም የግል የንግድ ድርጅቶች ቀጥረው የሚያሰሯቸው ሠራተኞች ላይ ሊወስዱ ስለሚችሉት እርምጃ እርግጠኛ አይደሉም፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያም የቫይረሱ መግባት ከተረጋገጠበት ጊዜ አንስቶ መንግስት ትምህርት ቤቶችን  እንዲዘጉ አድርጓል፡፡ በመቀጠልም ፍርድ ቤቶች በከፊል እንዲሁም የመንግስት ተቋማት በፈረቃ የሚሰሩበትን ሁኔታ አመቻችቷል፡፡ በሌሎች የንግድ ድርጅቶች ላይ በመንግስት ደረጃ የተሰጠ ትዕዛዝ ባይኖርም የንግድ እንቅስቃሴ በመቀዝቀዙ እንዲሁም ግለሰቦች በተቻላቸው አቅም ከቤት እንዳይወጡ እየተመከረ በመሆኑ ሥራ በአግባቡ እየተሰራ እና ድርጅቶች በፊት ያገኙ የነበረውን ገቢ እያስቀጠሉ ነው ለማለት አዳጋች ነው፡፡

በመሆኑም የግል የንግድ ተቋማት በተለይ በእንደዚህ አይነት አስገዳጅ የሆነ ሥራን ማሰራት፣ ገቢንም መሰብሰብ በማይቻልበት ወቅት ምን አይነት ሕጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ ይችላሉ? በሕጉ ላይ የተቀመጡ አማራጮች ምንድን ናቸው? አማራጮቹን ለመጠቀምስ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችስ ምን ምን ናቸው? የሚሉትን ነጥቦች ከአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 (አዋጁ) ድንጋጌዎች አንጻር በመቃኘት አሠሪዎች በሠራተኞቻቸው ላይ አላስፈላጊ እርምጃ እንዳይወስዱ፤ ሠራተኞችም የሥራ ዋስትናቸው እስከምን ድረስ ሊሆን እንደሚችል ተገንዝበው የራሳቸውን መብት እንዲያስከብሩ እና አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በማሰብ ይህን ጽሑፍ ተዘጋጅቷል፡፡

 

ከአቅም በላይ የሆኑ ከሥራ ውል የሚመነጩ መብትና ግዴታዎች እንዲታገዱ ሊያደርጉ የሚችሉ ሁኔታዎች፡-

Continue reading
  5206 Hits