ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል?

 ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል?

 

በእኛ ሀገር የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል? ተከሳሽ ምስክር መሆን አለመሆን ጥቅምና ጉዳቱ ምንድነው?

በአንድ ወቅት አንድ አስታጥቄ የሚባል ሰው ማረሚያ ቤት ልንጠይቀው ሔደን የተናገረውን አልረሳውም፡፡ ይኼው ጓደኛችን በስድብና ማዋረድ፣ ዛቻና የእጅ እልፊት ወንጀሎች ስድስት ወር ቀላል እስራት ተወስኖበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከወረደ በኋላ፤ በክርከሩ ሂደት መመስከርና ምስክር መሆን አትችልም መባሉ እንዳሳዘነው ሲነገረን ተደንቄ ነበር፡፡

በሀገራችን የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተከሳሽ ራሱ በተከሰሰበት ጉዳይ ምስክር መሆን እንደማይችል እንደ ዐቃቤ ሕግ እገነዘባለሁ፡፡ አንድ ተከሳሽ እንዲከላከል ከተበየነ በኃላ፣ የቆጠራቸው ምስክሮች ከመሰማታቸው በፊት የተከሳሽነት ቃሉን መስጠት ይችላል ነገር ግን ቃለ መኃላ አይፈጽምም፣ መስቀለኛ ጥያቄም አይጠየቅም፡፡ ባጭሩ ምስክር አይሆንም!

Continue reading
  9532 Hits
Tags:

ፍርድ ቤት ቅጣት ማቅለያን ወይም ማክበጃን በሌላ ማቅለያ ወይም ማክበጃ ቀይሮ ማቅለል ወይም ማክበድ ይችላል?

ፍርድ ቤት ቅጣት ማቅለያን ወይም ማክበጃን በሌላ ማቅለያ ወይም ማክበጃ ቀይሮ ማቅለል ወይም ማክበድ ይችላል?

የቅርብ ጓደኛው ጋር ተጠግቶ ይኖር የነበረ ግለሰብ፣ ጓደኛው በሌለበት አሳቻ ሰዓት 10000 ብር የሚገመት ቶሺባ ላፕቶፕ ወስዶ ለግል ጥቅሙ አውሏል በሚል የወንጀል ሕግ አንቀጽ 665(1)በመተላለፍ በስረቆት ወንጀል ተከሶ፣ ክሱን በዝርዝር በማመኑ ጥፋተኛ ይባላል::

የቅጣት ማክበጃ አስተያየት የተጠየቀው ዐቃቤ ሕግ የወንጀሉን ደረጃና እርከን ካስቀመጠ በኋላ “ተከሳሹ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመው አስጠግቶ በሚያኖረው የቅርብ ጓደኛው ላይ በመሆኑ በከሐዲነት የፈጸመው ነው፡፡ ስለሆነም በወንጀል ሕግ አንቀጽ 84(1)() መሠረት ከብዶአንድ ርከን ከፍ ብሎ  ይወሰንል” ብሎ ይጠይቃል::

ፍርድ ቤቱ የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያ አስተያየት ከሰማ በኋላ በሰጠው ዝርዝር ቅጣት ተታ ዐቃቤ ሕጉ አቅርቦ የነበረውን የቅጣት ማክበጃ በተመለከተ “ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው በከዲነት ሳይሆን የተጣለበትን እምነት ወይም ኃላፊነት ያላግባብ በመገልገል በመሆኑ በወንጀል ሕግ አንቀ 84(1)ሀ ሳይሆን በወንጀል ሕግ አንቀጽ 84(1)(ለ) መረት የቅጣት ማክበጃውን ቀይረን አክበደናል” ብሎ በመጨረሻተከሳሹ ላይ ሁለት ዓመት ቀላል እስራት ወስኖ መዝገቡን ይዘጋል::

በዚህ ባነሳሁት እውነተኛ የፍርድ ቤት ውሎ ፍርድ ቤቱ ቅጣት ማክበጃውን መቀየሩ አግባብ ነውወይስ አይደለም? የሚል ጥያቄ ፈጠረብኝ፡፡ አግባብ ከሆነስ በምን የግ መረት?

Continue reading
  10145 Hits
Tags:

ወስላትነት በኢትዮጵያ ሕግ ምን ማለት ነው

 ወስላትነት በኢትዮጵያ ሕግ ምን ማለት ነው

 

በአንድ ወቅት በፌደራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በታየ የስርቆት ወንጀል ጉዳይ ተከሳሹ ድርጊቱን መፈፀሙ ተረጋግጦ ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ፣ የቅጣት አስተያየቱን እንዲሰጥ የተጠየቀው ዐቃቤ ሕግ ‹‹…ተከሳሽ ድርጊቱን የፈፀመው መጥፎ አመልን በሚያሳይ ሁኔታ በወስላታነት…›› መሆኑን ለፍርድ ቤት በማስታወስ ቅጣቱ ከብዶ እንዲወሰን ይጠይቃል፡፡ ይሄንን የሰማው ተከሣሽም ዐቃቤ ሕጉን አቋርጦ ‹‹ኧረ የተከበረው ፍርድ ቤት ዐቃቤ ሕጉ ራሱ ወስላታ ነው፣ መቀጣቴ ካልቀረ መሰደቤ ለምን?›› ብሎ መከራከሩን ሰምቻለሁ፡፡

ለመሆኑ ወስላታነት ምንድን ነው? ‹‹አንተ ወስላታ!›› የሚለው ግሳፄ ዕድሜያቸው ከፍ ባሉ አባቶችና እናቶች ተደጋግሞ ሲነገር መቼም ሰምተን እናውቃለን፡፡ የከሣቴ ብርሃን መዝገበ ቃላት ስልትና ማለት ‹‹አለመታመን፣ የማታለል ድርጊት፣ ማጋጣነት ሥራ ፈትነት›› እንደሆነ ይገልፃል፡፡ በአጠቃላይ ኅብረተሰባችን ወስላታነትን በበጎ ጎኑ አይመለከተውም፣ ዛሬ በዚህች አጭር ጽሑፍ ወስላታነት በተለምዶ ከሚሰጠው ትርጉም በዘለለ በሕጋችን ያለውን ትርጓሜ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡

ቀደም ብሎ በዚህ ጽሑፍ መጀመሪያ ላይ በተጠቀሰው የችሎት አጋጣሚ ላይ ዐቃቤ ሕግ የቅጣት አስተያየቱን መሠረት ያደረገው የወንጀል ሕጉን አንቀጽ 84(1)ሀ ሲሆን ድንጋጌው ተከሳሾች ጥፋተኛ የተባሉበትን ወንጀል የፈፀሙት በከሐዲነት ወይመ በወስላታነት፣ ወራዳነትን ወይም መጥፎ አመልን በሚያሳይ ምቀኛነት፣ ጥላቻ፣ ስግብግብነት… ከሆነ ቅጣቱ ከብዶ የሚወሰንበትን አግባብ ይዘረዝራል፡፡

Continue reading
  11210 Hits
Tags: