ጣልያንን ለዘጠኝ ዓመታት የመሩት የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንትና ባለቤት እንዲሁም ቢሊየነሩ ሲልቪዮ ቤርሎስኮኒ በተከሰሱበት የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሚላን ከተማ የሚገኘው ፍርድ ቤት ቤርሎስኮኒ የአራት ዓመታት እስራት ቢፈረድባቸውም የእስራት ቅጣቱ በተለያዩ ምክንያቶች ቀርቶ በተቃራኒው ቤርሎስኮኒ በአረጋውያን ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ እ.ኤ.አ. በ2013 መወሰኑ ይታወቃል፡፡ በውሳኔው መሠረትም ቤርሎስኮኒ ሴሴኖ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና ከ2000 በላይ በእድሜያቸው የገፉ፣ የአእምሮና የአካል ጉዳተኛ የሆኑ አረጋውያን በሚገኙበት ማዕከል ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በሳምንት ለአራት ሠዓታት በማዕከሉ እየተገኙ አረጋውያኑን እንዲመግቡ፣ እንዲንከባከቡ፣ እንዲያንሸራሽሩ እንደ አጠቃላይም በማንኛውም መልኩ ከአረጋውያኑ ጎን እንዲሆኑ ተወስኖባቸው ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱን ፈፅመው አጠናቀዋል፡፡
Introduction
This commentary analyses two self-contradictory criminal cases decision of Federal Democratic Republic of Ethiopia (FDRE)Supreme Court cassation division (hereinafter referred as the division) that have equal legal value on all subordinate courts of Federal as well as Regional States to date. The central issue of these cases was the model of corporate criminal liability in Ethiopian criminal justice system.
መግቢያ
አንድን የወንጀል ተግባር በሕግ አግባብ አጣርቶና መርምሮ ወደ ፍርድ ሂደቱ ለማስገባትና ውሳኔ ለማሰጠት አስቀድመው ከሚከናወኑ ዐበይት ተግባራት መካከል የመጀመሪያው የወንጀል የምርመራ ሥራ ነው። በመሰረታዊነት የወንጀል የምርመራ ተግባርን የማከናወን ኃላፊነትና ሥልጣን የፖሊስና የዐቃቤ ሕግ መሆኑ ቢታወቅም በብዙ የሂደቱ ደረጃዎች ፍርድ ቤቶች ያላቸው ሚና ላቅ ያለ መሆኑም የሚታወቅ ነው። መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪውን በሕግ አግባብ መያዙን፣ ከያዘውም በኋላ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ፍርድ ቤት ማቅረቡን፣ የአቆያየት ሁኔታውን በተመለከተም በአግባቡ አይቶና መርምሮ ተገቢ ናቸው ያላቸውን ሕጋዊ ትዕዛዛትና የማስረጃ አሰባሰብ ጉዳዮችን (ለምሳሌ፡- የቀዳሚ ምርመራ፣ የመያዣና የብርበራ ትዕዛዛት…) ኹሉ በበላይነት በመምራትና በመቆጣጠር የግለሰቦችንና የህዝብን መብትና ጥቅም የማስከበር ኃላፊነት አለባቸው።
Abstract
22 July 1991 to 21 August 1995, and 21 August 1995 to present by Transitional Charter and Federal Democratic Republic of Ethiopia (FDRE) constitution, respectively, Ethiopia adopted a federal system and structured the regions along ethnic lines. And Oromia Regional State (ORS) is Ethiopia's most populous and largest region.
‘Write Your Injuries in Dust and Your Benefits in Marble’ – Benjamin Franklin.
Abstract
Though it needs statically documented data to conclude so, the practice demonstrates that bodily injury crime is one of the most frequently committed crimes. Nonetheless, there is no common worldwide standard to define what constitutes bodily injury crime and to classify bodily injury crime, particularly to grave bodily injury crime and common willful injury crime.
መግቢያ
በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በሚኖራቸውም ግንኙነት ግልፅ የሆነ የሚና ወይም የተግባር ልዩነት ሊኖራቸው የተገባ መሆኑም የሚታመን ነው። በዚህ መርህ ውስጥ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀምን በሚመለከት ቀዳሚ ኃላፊነት ከተሰጣቸው የመንግስት አካላት ውስጥ በተለይም የህግ አስፈፃሚው እና የህግ-ተርጓሚው ሚና በእጅጉ የሚልቅ ነው። እነዚህ ተቋማት በሌሎች ሀገራት ላይ ያላቸው መስተጋብር እና ጤናማ የሆነ ውድድር የዜጎች የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በተሻለ እንዲከበሩ አስተዋፅኦ አድርጓል።
መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ
በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም የተበዳይ ተወካይና ቤተዘመዶች በደል ካደረሰባቸው ሰው ፍትሕን በገዛ እጃቸው ያገኙ ነበር። ተበዳይ ጥቃት ያደረሰበትን ሰው ሲፈልግ ይበቀላል፣ ሲፈልግ በፍርድ አደባባይ ይከሳል ወይም ለደረሰበት በደል ከተበዳይ ከሳ ይቀበላል። አይ ይህን ሁሉ አልፈልግም ካለም ከሁሉም ታቅቦ ፍትሕን ከእግዚአብሔር እየጠየቀ ይኖራል። በዚህ ጊዜ ምርመራ አጣርቶ ክስ የሚመሰርት የዐቃቤ ሕግ ተቋም በሀገሪቱ አልነበረም። በግለሰቦች መሀከል የሚፈጠር አለመግባባቶችን ‹‹የወንጀል›› ጉዳይ እና የግለሰቦች የፍትሐብሔር ጉዳይ ብሎ የሚከፋፍል የሕግ ስርአት ባለመኖሩ ጥቂት በሀይማኖትና በመንግስት ላይ የሚፈፀሙ በአሁኑ ሰአት የፓለቲካ ወንጀል እየተባሉ ከሚጠሩ ወንጀሎች በስተቀር ሁሉም አለመግባባቶች ላይ ግለሰቦች በራሳቸው ከሳሽ በመሆን ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ያቀርባሉ ወይም ፍትሕን በእጃቸው ያገኙ ነበር። ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዱ ከሆነ ክስ የመመስረት፣ የተጀመረን ክስ የሟቋረጥ፣ ቅጣትን በመምረጥ ተበዳይ ግለሰብ ሁሉን አድራጊ ነበር። የወንጀል ይዘት ያላቸው ጉዳዮችን ከፍትሀብሔር ጉዳዮች ጋር በማጣመር የጉዳት ካሳን መጠየቅም ይቻል ነበር። በዘመኑ የወንጀል ተበዳዮች በወንጀል ጉዳይ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች ነበሩ።
መንግሥት የሃገርን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ እና የማስጠበቅ እንዲሁም የሕዝቦቹን እና የነዋሪዎቹን መሠረታዊ የግለሰብና የቡድን ነፃነት መብት እና ጥቅም የማክበርና የማረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነትና ሚና አለበት፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል በግልጽ በሚመራ ሥርዓት የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን መዘርጋትና ማቋቋም አንዱና ዋነኛው ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ማዕቀፍን ከሚያቋቁሙ ምሰሶዎች መካከል የወንጀል ሕግ፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት ሕግ እና የማስረጃ ሕግ በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡