ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል?
በእኛ ሀገር የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል? ተከሳሽ ምስክር መሆን አለመሆን ጥቅምና ጉዳቱ ምንድነው?
በአንድ ወቅት አንድ አስታጥቄ የሚባል ሰው ማረሚያ ቤት ልንጠይቀው ሔደን የተናገረውን አልረሳውም፡፡ ይኼው ጓደኛችን በስድብና ማዋረድ፣ ዛቻና የእጅ እልፊት ወንጀሎች ስድስት ወር ቀላል እስራት ተወስኖበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከወረደ በኋላ፤ በክርከሩ ሂደት መመስከርና ምስክር መሆን አትችልም መባሉ እንዳሳዘነው ሲነገረን ተደንቄ ነበር፡፡
በሀገራችን የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተከሳሽ ራሱ በተከሰሰበት ጉዳይ ምስክር መሆን እንደማይችል እንደ ዐቃቤ ሕግ እገነዘባለሁ፡፡ አንድ ተከሳሽ እንዲከላከል ከተበየነ በኃላ፣ የቆጠራቸው ምስክሮች ከመሰማታቸው በፊት የተከሳሽነት ቃሉን መስጠት ይችላል ነገር ግን ቃለ መኃላ አይፈጽምም፣ መስቀለኛ ጥያቄም አይጠየቅም፡፡ ባጭሩ ምስክር አይሆንም!