ጦማሪው ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት በ2007 ዓ.ም በሕግ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ ሲሆን አሁን በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤቶች በሕግ አማካሪና በጠበቃነት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡

ጸሐፊውን mulukenseid29@gmail.com ወይም +251917324914 ማግኘት ይችላሉ፡፡

Updates on the recent administrative procedure proclamation no 1183/2020

Before the enactments of the Federal Administrative Procedure Proclamation, there is a gap in the Ethiopian legal regime due to the absence of administrative procedure law. This is a neglected subject both by the legal academia and practitioners. It is very difficult and challenges to talk about the history of administrative law in Ethiopia. Administrative law is still not well developed, and it is an area of law characterized by the lack of legislative reform.

  8229 Hits

የውርስ ኃብት ማጣራትን የተመለከቱ አንዳንድ ነጥቦች ከሰበር ውሳኔ ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

የውርስ ህግ ክፍል በሆነው የፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 826 ላይ እንደተመላከተው አንድ ሰው የሞተ አንደሆነ በሞተበት ጊዜ ዋናው መኖሪያው በሆነበት ስፍራ የዚህ የሟች የውርስ ሀብት ይከፈታል፡፡ የሟች ውርስ ሟች በሞተበት ቅጽበት የሚከፈት ቢሆንም የሟች የውርስ ሀብት እስከሚጣራ ድረስ የሟች ንብረት እንደ አንድ የተለየ ንብረት ይቆጠራል፡፡ ይህም ማለት የሟች ንብረት ከሌሎች ሰዎች ወይም ወራሾች ንብረት ጋር ሳይቀላቀል የባለቤትነት መብቱ ለወራሾች ሳይተላለፍ እንደ አንድ ልዩ ንብረት ሆኖ ሊያዝ እንደሚገባ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 942 ይደነግጋል፡፡

  20847 Hits

የውርስ ጉዳይን የተመለከቱ የይርጋ ገደቦች

ማንኛውም ሰው አንድ የፍርድ ውሰኔ ሊያገኝ የሚገባ ጉዳይ ያለው እንደሆነ ጉዳዩን ለማየት በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ሊያቀርብ ሚችልበት የጊዜ ገደብ በልዩ ልዩ የሕግ ድንጋጌዎች ላይ ተመልክቶ ይገኛል፡፡ ይህን መሰል የጊዜ ገደብ በሕግ አጠራር ይርጋ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ትርጓሜውም በሕግ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ባለመብት የሆነ ወገን መብቱን ለመጠየቅ ተገቢውን ትጋት ማድረግና የመብት ጥያቄውን ማቅረብ ያለበት ሲሆን ይሄን ሳያደርግ ቢቀር ግን መብቱ በይርጋ (በጊዜ ገደብ) ቀሪ የሚሆን ይሆናል የሚል ነው፡፡

  26928 Hits

በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

  15974 Hits