Abyssinia Law is a legal resource portal providing open access to primary and secondary legal materials for Ethiopia, such as laws, court decisions, articles, contact guidance, and Lawyers Directory - with texts supplemented by online videos, a discussion forum, and a user blog. The service gives free access to Federal and State consolidated laws of Ethiopia (with status information on whether the law is amended, repealed, or effective)

በኢትዮጵያ የብድር ሕግ "አበደረ" ማለት የብድሩን ገንዘብ ሰጠ ማለት ይሆን?

በዚህ በኩል ግቡ

ብድር የሰው ልጅ እና ጎደሎው ከተገናኙበት ሩቅ ዘመን ጀምሮ የነበረ ሰዋዊ ድርጊት ነው፡፡ የብድር መሰረቶቹ መቀራረብ፣ እዝነት እና መተማመን ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን እነዚህ መሰረቶቹ እየተናጉ የብድርን ህልውና ሲፈታተኑት ይስተዋላል፡፡ በርካታ ሰዎችም ብድርን መሰረት ላደረጉ ክርክሮች ሲዳረጉ ይታያሉ፡፡

ከእነዚህ በርካታ ብድር ነክ ክርክሮች አንዱ በውሉ ላይ ተበዳሪ ተብለው የተሰየሙ ሰዎች የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም በማለት የሚያነሱት ክርክር ነው፡፡ ተበዳሪው በውሉ ላይ ተበድሬአለሁ ብሎ የፈረመ ቢሆንም ውሉ ፍ/ቤት ሲመጣ ግን ተበድሬአለሁ ብዬ ፈርሜአለሁ ግን የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም ማለት ይከራከራል፡፡

Continue reading
  4588 Hits

A dreamless dreamer: should pauper proceeding be allowed in Arbitration proceeding?

 

The legislator who, on the plea of checking litigation, or on any other plea, exacts of a working man as a preliminary to his obtaining justice, what that working man is unable to pay, does refuse to him a hearing, does, in a word, refuse him justice, and that as effectually and completely as it is possible to refuse it. - Jeremy Bentham (A Protest Against Law Taxes)

 

Meaning and grounds for filing a pauper proceeding

 

Continue reading
  4318 Hits

Snapshot Review of Imperative Necessity and challenges for Implementation IHL: Part Two

 

 

1. Problems of Implementation in International Humanitarian Law

 

Failure to implement IHL is conceived as a central problem in contemporary armed conflict laws in general and Ethiopia in particular. However, it must be noted that difficulties regarding securing compliance is not something that is unique to the law of armed conflict, but also an issue in international law. This problem by large is related to the lack of a central enforceable organ that looks after the implementation of those laws.

Continue reading
  3641 Hits

Snapshot Review of Imperative Necessity and challenges for Implementation IHL: Part One

 

 

Synopsis

The implementation of the International Humanitarian Law (hereinafter referred to as IHL) mainly rests upon the effort of the state parties. The international humanitarian law is currently accepted by every country in the world but the absence of a comprehensive and meticulous mechanism to enforce the rules embodied in IHL, is an Achilles’ heel fuelled by the very nature of IHL which is meant to regulate the issues that arise out of armed conflict.

Where there is an existing issue that causes harm, once recognized a law is set in that specific area to govern or to address that issue. This could be so as to minimize the damage that the issue causes, to prohibit that act from being committed or it could also be just to manage or set a guideline as to how those acts should be committed. Armed conflict or war is a commonly known phenomenon that causes great destruction.

Continue reading
  3642 Hits

የፍርድ ቤቶች በከፊል መዘጋት በማረምያ ቤት ከሚገኙ እስረኞች መብት አንጻር

 

 

የኮሮና (COVID-19) በሽታ አለም አቀፍ ችግር ሆኗል፡፡ በአለም ላይ ያሉ ሳይንቲስቶች በደረሱበት የምርምር ደረጃም በትክክል የሚተላለፍባቸው መንገዶች በሙሉ ተለይተው አይታወቁም፡፡ ነገር ግን በሽታው በሰዎች መካከል በሚኖር ቀጥተኝ (መጨባበጥ፤ መተቃቀፍ..) እና ቀጥተኛ ያልሆነ (አንድ ሰው የነካውን ግኡዝ ነገር ሌላ ሰው በመንካት …) አካላዊ ንክኪ እና የትንፋሽ ግንኙነት በቀላሉ የሚተላለፍ መሆኑ በትክክል ይታወቃል፡፡ ይህ ከሰዎች ባሕሪ ጋር በቀጥታ የተገናኘ የመተላለፍያ መንገዱ በሽታውን እጅግ አደገኛ እና አስፈሪ አድርጎታል፡፡ በሽታው ምንም አይነት ፈዋሽ መድሀኒት የሌለው መሆኑ እና ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍበት እና የሚሰራጭበት ፍጥነት በድምር ሲታይ ብሔራዊ ስጋት ተደርጎ እንዲወሰድ አድርጎታል፡፡ በበሽታው የተፈጠረው ብሔራዊ ስጋት ተራ ስጋት ሳይሆን ከፍተኛ እና ከባድ ስጋት ነው፡፡   

በሽታው ምንም አይነት ፈዋሽ መድሀኒት የሌለው ከመሆኑ አንፃር ያለው ብቸኛ መዳኛ መንገድ በበሽታው ላለመያዝ አስቀድሞ የሚደረግ የመከላከል ተግባራትን መፈፀም ብቻ ነው፡፡ የሕክምና ባለሙያዎች ከበሽታው አስቀድሞ መከላከያ መንገዶች አድርገው በዋናነት የሚጠቅሷቸው ዘዴዎች አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና ንፅህናን መጠበቅ ናቸው፡፡

አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የሚለው የመከላከያ ዘዴ ሰዎች በቤታቸው ተቀምጠው ራሳቸውን ከሌላው ሕብረተሰብ ከልለው እንዲቀመጡ ከማድረግ ጀምሮ በስራ፤ በትራንስፖርት እና በሌሎች አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥም ቢያንስ የሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ርቀትን በማስጠበቅ እንዲንቀሳቀሱ እና አገልግሎት እንዲገኙ ማድረግን የግድ ይላል፡፡ ይህን በከተማ ብሎም በሀገር ደረጃ ተግባራዊ ማድረግ እና ተግባራዊነቱን መከታተል እና መቆጣጠር ቀላል ተግባር አይደለም፡፡ በዚሕ መሀከል የሚፈፀም ትንሽ ስህተት ተቆጥሮ የማያልቅ የብዙ ሰዎችን ሕይወት የሚቀጥፍ ወይም አደጋ ላይ የሚጥል ውጤት ሊያስከትል ይችላል፡፡

Continue reading
  5084 Hits

በኮሮና ወረርሽኝ ፍርድ ቤቶችን እንዴት ማስቀጠል ይቻላል?

 

እርግጥ ነው አሁን ያለንበት የኮሮና ቫይርስ ወረርሽኝ ወቅት እጅግ ፈታኝ፣ ፈጣን አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመስጠት የሚከብድበት የቱ ትክክልየቱ ስህተት እንደሆነ ለማመዛዘን የሚቸግር ጊዜ ነው፡፡ በተለይም በወረርሽኙ ምክንያት የሰዎች ህይወት አደጋ ላይ መውደቁ ሲታይ አሳሳቢና አስጨናቂ ነው፡፡

በዛው መጠን ደግሞ በማዕበሉ ወቅትም ቢሆን ህዝብና የመንግሥት አስተዳደር ይቀጥላል፡፡ ፍርድ ቤቶች ደግሞ እጅግ በጣም አስፈላጊና ወሳኝየህዝብ አገልግሎት ሰጪ አካላት መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ሐቅነው፡፡ ፍ/ቤቶች ከሶስቱ የመንግሥት አካላት (the three organs of Government/state) አንደኛው ቅርንጫፍ/አካል ናቸው፡፡ ሌሎቹ የመንግሥት አካላት(አስፈፃሚውና ሕግ አውጪው) ሥራቸውን እያስኬዱ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በወረርሽኙ ምክንያት የሰውን ህይወት ለአደጋ በማያጋልጥና በጥንቃቄ ሥራቸውን የሚያስኬዱበት መንገድ ሊፈተሸ ይገባል፡፡

በጣም የሚያስደነግጠው ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ‹‹የኮሮና ቫይረስ ለማጥፋት በርካታ ዓመታት ሊወስድ ይችላል፡፡ የሚጠፋበት ጊዜ ቅርብ አይደለም እንደውም እንደ ኤች.አይ.ቪ ላይጠፋ ይችላል›› የሚል መግለጫን አውጥቷል፡፡

ስለዚህ ፍርድ ቤቶችም ሆኑ ሌሎች ወሳኝ አገልግሎት ሰጪ አካላት በቀጣይ ከቫይረሱ ጋር በጥንቃቄ ህይወት የሚቀጥልበትን መንገድ ሊያስቡበት ግድ ይላቸዋል ማለት ነው፡፡ እጅን አጣጥፎ ‹‹ጥሩ ቀን ቶሎ ና›› እያሉ ብቻ መጠበቅ አያስኬድም አያዋጣም፡፡

Continue reading
  4611 Hits

የፍርድ አፈፃፀም መሠረታዊ ታሳቢዎችና ያጋጠሙ ችግሮች

 

 

አፈፃፀም ፍርድ ቤት የሰጠውን ፍርድ በእራሱ አማካኝነት ወደ ተግባር የሚለውጥበት ሥርዓት ነው፡፡ ስለፍርድ አፈፃፀም የተደነገጉትን ድንጋጌዎች በመከተል ፍርድን በተግባር መተርጎም እንደመሆኑ መጠን የማስፈፀሚያ ሥርዓቱ በጥቅሉ የፍ/ብ/ሥ/ሥ ህጉን መሠረታዊ ዓላማ ተከትሎ በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲፈፀም በሚያስችል አኳኋን የተዋቀረ ነው፡፡

ይሁን እንጂ በተግባር እንደሚታየው ክስ አቅርቦ ለማስፈረድ ከሚወሰደው ውጭ ጊዜና ጉልበት ባልተናነሰ ሁኔታ የተፈረደን ፍርድ ለማስፈፀም የሚጠይቀው ወጭና ጊዜ በልጦ የሚታይበት ጊዜ ይከሰታል፡፡ ምክንያቶቹ በርካታ ናቸው፡፡

ከነዚህም ጥቂቶቹ፡-

Continue reading
  17422 Hits

ሕዝባዊ ፍርድ፣ ፍርድ ቤቶች እና ገላጋይ ዳኞች

 

የፍርድ ቤቶችን ችግር ለመፍታት፣ ጫናቸዉን ለመቀነስ፣ የሚያቀርቡትን የዳኝነት አገልግሎት ጥራት ለመጨመር ከሚቀርቡት የመፍትሄ ሃሳቦች መካከል አማራጭ የሙግት መፍቻ ስልቶችን (ለምሳሌ ግልግል ዳኝነት) ማበረታት ነዉ።

አማራጭ ስልቶችን ማበረታታት ተገቢ ነዉ፣ ጠቃሚ እስከሆነ ድረስ።  ነገር ግን ፍርድ ቤቶች በችግሮች በተተበተቡበት ሁኔታ፣ ምንም እንኳን ሕጉ ለአማራጭ ስልቶች እውቅና እና ድጋፍ ቢሰጥም፣ የፍድ ቤቶችን ችግር በመፍታት ወይም አለመግባባትን በመቀነስና በመፍታት ረገድ ግን የሚፈይደው ነገር ጥቂት ነው፡፡

የፍርድ ቤቶች መጠናከር ነዉ ቅድሚያ ሊስጠዉ የሚገባዉ። ፍርድ ቤቶች ሲጠናከሩ (ለምሳሌ በፍጥነት ዉሳኔ ሲሰጡ፣ ዉሳኔዎቻቸዉ ግልጽ፣ ተደራሽ፣ ተገማች ሲሆኑ፤ ሙስና ሲቀንስ) ብቻ ነዉ፤ ግለሰቦችና ድርጅቶች ሌሎች አማራጭ የግጭት መፍቻ ስልቶችን ሊጠቀሙ የሚችሉት። ፍርድ ቤት ቢሄዱ፤ መቼ፣ እና ምን አይነት ዉሳኔ፣ በምን ዋጋ ማግኘት እንደሚችሉ መገመት ሲችሉ ብቻ ነዉ አማራጭ መንገዶችን ለመጠቀም ሊወስኑ የሚችሉት።

ወደ ፍርድ ቤት ነዉ የሚሄዱት። ፍርድ ቤቶችራሳቸዉ በችግሮች በተተበተቡበት ሁኔታ፣ ምንም እንኳን አንደኛዉ ወገን ዉጭ በገላጋይ ዳኞች መዳኘት ቢፈልገም፣ ሌላኛው በተለይ ደግሞ የፍርድ ቤቶችን ችግር የሚፈልገው ላይስማማ ይችላል፡፡ በዚህም የበለጠ ፍርድ ቤት እንዲጨናነቅ ያደርገል፡፡

Continue reading
  9547 Hits

የግብይት ወጪ በግብርና

 

የግብይት እና የምርት ወጪ የሚባሉ ሁለት መሰረታዊ ወጪዎች አሉ። የምርት ወጪ የምትለው፥ አንድን አገልግሎት ወይም ሸቀጥ ወይም ነገር ለማምረት የምታወጣው ነው። ቋሚ እና ተቀያያሪ ወጪ ሊሆን ይችላል። ቋሚ የሚባለው ወጪ መጠን፥ በምርትህ መጠን አይወሰነም እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ። ስለዚህ አንድም አመረትህ ሺተሚሊዮን ቋሚ ወጪዉ ተመሳሳይ ነው። ስለዚህ ብዙ ማምረት ከመጠን እንድትጠቀም ያደርግሃል። ነገር ግን ምን ታመርታለህ? ምንድን ነው ፍላጎትህ? ያመረትከውንስ ለማን እና በምን ያህል ትሸጣልህ? ግብይት ከማን ጋር ትፈጽማለህ? በድርድር ሂደት ያኛው ተዋዋይ ወገን የሚነግርህን መረጃ እንዴት ታረጋግጣለህ? ያኛው ሰውየ ያልነገረህ መረጃ ስለመኖሩ እንዴት ታረጋግጣለህ? እንዴት ትደዳደራለህ? ስምምነት ከገባህ በዃላ ያኛው ሰው ግዴታውን ለመወጣቱ ምን ማረጋገጫ አለህ? ግዴታውንስ በተባለው መጠን እና ጥራት ስለመወጣቱ እንዴት ትከታተላለህ? እነዚህ ሁሉ የግብይት ወጪ ይባላሉ።

ሁለቱ አይነት ወጪዎች ይገናኛሉ። የግብይት ወጪ መናር፥ ግብይት እንዲቀንስ ያደርጋል። ግብይት አነስተኛ ሲሆን፥ ምርት ይቀንሳል። ምክንያቱም ምርት የሚጨምረው ስፔሻላይዜሽን ሲኖር ነው። ነገር ግን የግብይት ወጪ መናር ስፔሻላይዤሽን እንዲቀንስ ያደርጋል። አንድ ምርት ላይ ብቻ አተኩረህ፥ በዚህም ምርትህን በጣም ልትጨምር ትችላለህ። ነገር ግን ሁሉንም ምርት ለግል ፍጆታህ ላትፈልገው ትችላለህ። እንዲሁም፥ የአንተ ፍላጎት አይነት በአንድ ምርት ብቻ ላይገደብ ይችላል። ሌሎች ብዙ የምትፈልጋቸው ነገሮች ይኖራሉ። ችግር የለውም፥ ትርፍ ምርትህን ሸጠህ፥ አንተ ያላመረትከውን ነገር ግን የምትፈልጋቸውን ነገሮች ከሌላ ትገበያለህ። ይህን የምታደርገው ግን የግብይት ወጪዉ አነስተኛ ከሆነ ነው። የግብይት ወጪዉ ከፍተኛ ከሆነ፥ የምትፈልገውን ወጪ በሙሉ ራስህ ለማምረት ትሞክራለህ። በዚህም ሁሉም ፍላጎትህ በመጠኑ ይሟላል። ነገር ግን በአይነትና በመጠን የማይሟሉ ፍላጎቶች ይኖርሃል።

የግብርና ክፍለኤኮኖሚ ባብዛኛው ከእጅ ወደ አፍ ነው።  አብዛኛው አርብቶ እና አርሶ አደር ከብትም ያረባል፥ ከሰብል ምርትም ከሁሉም አይነት ለማምረት ይሞክራል። ጥያቄው ምርትን እንዴት እንጨምር የሚል ነው?

ባብዛኛው ትኩረታችን እንዴት አድርገን የምርት ወጪውን እንቀንስለት የሚል ነው። አርሶ አደሩ የሚፈልገውን ግብአት በሚፈለገው መጠን እና አይነት እና ጥራት ማቅረብ። ስለዚህ የግብርና እውቀት፥ መስኖ፥ ጤና፥ የመጠጥ ዉሃ፥ ማዳበሪያ፥ ምርጥ ዘር፥ ትራክተር፥ ማጨጃ፥ መውቂያ፥ ሰውሰራሽ የከብት እርባት ቴክኖሎጂ፥ የከብት ህክምና አገልግሎት፥ የአየር ሁኔታ ትንበያ፥ እና የመሳሰሉትን የምርት ወጪ መቀነሻ ወይም የምርት መጨመሪያ ግብአቶችን ማቅረብ እንደ መፍትሄ ተወስዶ እየቀረበ ነው።

Continue reading
  7818 Hits

የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ፤ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሕግ የማውጣት ሥልጣን እና የአስተዳደሩ ተጠሪነት ጉዳይ

 

 

የዚህ አጭር ጽሑፍ ዋና ትኩረቱን በድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/1996 ላይ በማድረግ አዋጁ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት በአንቀፅ 55(1) ላይ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ከተሰጠው ሕግ የማውጣት ስልጣን ጋር ያለውን ተቃርኖ እና የሕገ መንግስቱን የበላይነት ያላከበረ ስለመሆኑ እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ተጠሪነት ላይ የሚነሱ የሕግ ጉዳዮችን በመዳሰስ መፍትሔውን ማስቀመጥ ነው፡፡

በአስራ አንድ ምዕራፎች እና በአንድ መቶ ስድስት አንቀጾች የተዋቀረው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት ህዳር 29 ቀን 1987ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በተወካዮቻቸው አማካኝነት አፅድቀውት ከነሐሴ 15 ቀን 1987 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ስራ ላይ እንደዋለ ከሕገ መንግስቱ መግቢያ እና በአንቀፅ 2 ላይ የተገጾ የምናገኘው ሲሆን ሕገ መንግስቱ በምእራፍ አራት እና አምስት ስለመንግስታዊ አወቃቀር እንዲሁም ስለሥልጣን አወቃቀርና ክፍፍል በሚገልፀው ክፍል ደግሞ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ስርዓተ መንግስት ፓርላሜንታዊ እንደሆነ፤ በፌዴራል መንግስት እና በክልሎች የተዋቀረ እንደሆነ፤ ክልሎቹም ዘጠኝ (ትግራይ፤ አፋር፤ አማራ፤ ኦሮሚያ፤ ሶማሌ፤ ቤንሻንጉል/ጉሙዝ፤ ደቡብ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፤ የጋምቤላ ሕዝቦች እና የሐረሪ ሕዝብ ክልል) እንደሆኑ፤ አዲስ አበባም የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ እንደሆነችና የከተማ አስተዳደሩም ተጠሪነቱ ለፌዴራል መንግሰቱ ሆኖ ዝርዝሩ በሕግ የሚወሰን እራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም በአንቀፅ 51 ላይ የፌዴራሉን መንግስት ስልጣን እና ተግባር የሚዘረዝር ሲሆን በአንቀፅ 55(1) ላይ ደግሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሕገ መንግስቱ ለፌዴራሉ መንግስት በተሰጠው የስልጣን ክልል ሕጎችን እንደሚያወጣ ይገልፃል፡፡

Continue reading
  9536 Hits