The blogger graduated from Hawassa University with LLB in 2017 and LLM in Commercial Law in 2019. He has been working as a lawyer in different governmental institutions, and since 2019, he has been a senior lawyer at the Federal Ministry of Revenues.

የማዕድን ሥራዎች ፈቃድ የተሰጠው ሰው እና በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ ንዑስ-ሥራ ተቋራጭ የግብር ግዴታ

መግቢያ

ማንኛውም ገቢ የሚያገኝ ሰው በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 እና በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 መሰረት ግብር የመክፈል ኃላፊነት አለበት፡፡[1] በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም የኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት፤ በኢትዮጵያ ነዋሪ ላልሆነ ሰው የትርፍ ድርሻ፣ የንዑስ ሥራ ተቋራጭ፣ የወለድ፣ የሮያሊቲ፣ የሥራ አመራር፣ የቴክኒካል፣ የመድን አረቦን፣ ወደ ውጭ አገር የሚላክ ትርፍ፣ እንዲሁም የሌሎች ገቢዎች ክፍያ ሲፈጽሙ ከጠቅላላ ክፍያው ላይ በግብር ሕጉ መጣኔ መሰረት ግብር ቀንሰው መያዝ እንዳለባቸው ተደንግጓል፡፡[2] በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ነዋሪ የሆነ ሰው ወይም በኢትዮጵያ ነዋሪ ያልሆነ በቋሚነት የሚሰራ ድርጅት ከመቀጠር ከሚገኝ ገቢ፣ ከትርፍ ድርሻ ወይም ካልተከፋፈለ ትርፍ፣ ከወለድ፣ ከሮያሊቲ፣ እና ከሌላ በአገር ውስጥ ከሚፈጸም ክፍያ ላይ በግብር ሕጉ መጣኔ መሰረት ግብር ቀንሰው መያዝ አለባቸው፡፡[3]

Continue reading
  2227 Hits