የርዕሰ መዲናዋን አስተዳደር ለመመስረት በቻርተር ደረጃ የወጣው አዋጅ ቁጥር 361/95 አንቀጽ 41(1) (ሸ) እና ማሻሻያው አዋጅ ቁጥር 408/96 አንቀጽ 2 የወራሽነት ማረጋገጫን ጨምሮ ሌሎች ምስክር ወረቀቶች የመስጠት የስረ ነገር ስልጣንን ለአዲስ አበባ ከተማ ፍ/ቤቶች ሰጥቷል። በዚህም መሰረት ከሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት ዓመተ ምህረት ጀምሮ እስካሁን ድረስ እነዚህ ፍ/ቤቶች እገሌ የእገሌ ወራሽ ነው፣ አንቺ የእንትና ሚስት ነበርሽ፣ አንተ ደግሞ የእገሊት አበዋራ ነበርክ …….. ወዘተ እያሉ በሕግ ዓይን ህያው ይሆን ዘንድ በሞት የፈረሰን የዓይነ ስጋ ዝምድና በወረቀት ማረጋገጫ ሲቀጥሉ ኖረዋል።
ብድር የሰው ልጅ እና ጎደሎው ከተገናኙበት ሩቅ ዘመን ጀምሮ የነበረ ሰዋዊ ድርጊት ነው፡፡ የብድር መሰረቶቹ መቀራረብ ፣ እዝነት እና መተማመን ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን እነዚህ መሰረቶቹ እየተናጉ የብድርን ህልውና ሲፈታተኑት ይስተዋላል፡፡ በርካታ ሰዎችም ብድርን መሰረት ላደረጉ ክርክሮች ሲዳረጉ ይታያሉ፡፡
ከእነዚህ በርካታ ብድር ነክ ክርክሮች አንዱ በውሉ ላይ ተበዳሪ ተብለው የተሰየሙ ሰዎች የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም በማለት የሚያነሱት ክርክር ነው፡፡ ተበዳሪው በውሉ ላይ ተበድሬአለሁ ብሎ የፈረመ ቢሆንም ውሉ ፍ/ቤት ሲመጣ ግን ተበድሬአለሁ ብዬ ፈርሜአለሁ ግን የብድሩን ገንዘብ አልተቀበልኩም ማለት ይከራከራል፡፡