Latest blog posts

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ምንድንነው? በወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 760/2012) መሠረት ምዝገባ ዘንድሮ መጀመር ያለበት ቢሆንም ምዝገባ እስካሁን ለምን አልተጀመረም? በአዋጅ የተቋቋመው ኤጀንሲ ምን በመስራት ላይ ነው? ምዝገባው መቼ ይጀመር ይሆን? የሚሉትና ሌሎች ጉዳዮችን ከኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ነፃነት ጋር አዲስ ዘመን ቆይታ በማድረግ የሚከተለውን አስነብቧል፡፡

አዲስ ዘመን፦ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ምንድንነው? የሚሰጠው ጠቀሜታስ?

ወይዘሮ ነፃነት፦ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ የሞት፣ ልደት፣ ጋብቻና ፍችን የመመዝገብ ሥራ ነው። የምዝገባው ጠቀሜታ ሦስት ዋና ጥቅሞች አሉት። ለኢኮኖሚያዊ፣ ለማህበራዊ አገልግሎት፣ ለሕግና ለሕዝብ አስተዳደር አገልግሎት ይውላል።

ለኢኮኖሚና ማህበራዊ አገልግሎት ሲባል በአገሪቱ የሚታቀዱ ፖሊሲዎችና እቅዶች መሠረት የሚያደርጉት የኩነቶችን መረጃ ነው። ለምሳሌ ትምህርት ቤቶችን፣ ሆስፒታሎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን ለመገንባት መነሻ የሚሆነው የአካባቢው ሕዝብ ነው። ትክክለኛ የሕዝብ ቁጥርን መረዳት የሚቻለው በዓመታት ልዩነት የሕዝብ ቆጠራ በማካሄድ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃና ሰከንድ የሚከሰቱ ኩነቶችን በመመዝገብ ነው።

ከሕግ አንጻርም በማስረጃ እጦት በሀሰት ምስክር ኢኮኖሚያዊ መብት የሚታጣባቸው በርካታ አጋጣሚዎች አሉ። አንዱን እንኳ ብንመለከት ልጅነትን መካድ አንዱ ነው። ልጆች የቤተሰ ቦቻቸውን ንብረት በእኩል የማግኘት መብት እያላቸው በመረጃ ባለመኖሩ በአንድ ቤተሰብ አንዱ ተጠቃሚ ሌላው ተጎጂ ይሆናሉ። ምዝገባው ይህን ያስቀረዋል። የሕዝብ አስተዳደርን በተመለከተ ለምርጫ፣ ለበጀት ድልድልና ለተለያዩ የሕዝብ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል።

አዲስ ዘመን፦ባለፉት ጊዜያት የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ይካሄድ ነበር። ለምን ኤጀንሲ ማቋቋም አስፈለገ?

ወይዘሮ ነፃነት፦ ከአሁን በፊት ምዝገባ ይካሄድ የነበረው በአዲስ አበባና በተወሰኑ የክልል ከተሞች ነው። አስገዳጅ ሕግ የለውም። በአገልግሎት ጠያቂው በኅብረተሰብ ፈላጊነት ብቻ የሚካሄደው ነው። የሞት፣የልደት የፍችና የጋብቻ ባለጉዳዩ ፈልጎ ሲመጣ ነው የሚሰጠው። አሁን ግን የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በከተሞች ብቻ ተንጠልጥሎ የሚቀር ሳይሆን በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ተግባራዊ የሚደረግ ነው።

አዲስ ዘመን፦ ኤጀንሲው ሲቋቋም በአዋጅ የተሰጡት ኃላፊነቶች አሉ። ምን ያህል ተወጥቷቸዋል?

ወይዘሮ ነፃነት፦ የወሳኝ ኩነቶች በአገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመር ግዙፍ ሥራ ያስፈልጋል። ይህን ግዙፍ ሥራ ለመስራት አዋጁ ባስቀመጠው መሠረት ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል።

በ2006 ዓ.ም የኤጀንሲውን ዋና ዋና የሥራ ሂደቶችን በጥናት በመለየት የማዋቀር፤ አስፈላጊ የሰው ኃይል የማሟላት ሥራ፤ ኤጀንሲውን በምክር ቤትና በቦርድ እንዲመራ አዋጁ ያስቀምጣል። እነዚህን ማደራጀት፤ ለቢሮ የሚያስፈልጉ ቁሳቁስና ቢሮ የማደራጀት ስንሰራ ነው የቆየነው። ኤጀንሲውን በሁለት እግሩ አቁመናል።

ራሱን ከማቋቋም ባለፈ ክልሎች የየራሳቸውን የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ እንዲያቋቁሙ የማስተባበርና የመደገፍ ኃላፊነትን ተወጥቷል። ለሁሉም የሚሆን መነሻ የማቋቋሚያ አዋጁ ሰርቶ ሰጥቷል። ወጥ የሆነ መረጃ ለማሰባሰብ የሚያስችል ደንብ ተዘጋጅቶ ለሁሉም ክልሎች ተልኳል። በፌዴራል ደረጃ የወጣውን መሠረት በማድረግ ክልሎች የራሳቸውን ተጨባጭ ሁኔታ ጨምረው ደንብ አውጥተዋል። ከቀበሌ ጀምሮ የሚኖራቸውን መዋቅርና የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ምን ዓይነት መሆን እንደሚገባቸው የሚመለከቱ አጫጭር ስልጠናዎች ተካሂደዋል።

የዘንድሮውን ዓመት የዝግጅት ጊዜ አድርገን ነው የወሰድነው። ኩነቶችን ለመመዝገብ የሚያስችሉ መመሪያዎችን እያዘጋጀን ነው። የአቅም ግንባታ ሥራ ከቀበሌ ጀምሮም እንሰራለን። ኩነቶችን እንዲመዘግቡ ኃላፊነት የተሰጣቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የመከላከያ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት ድርጅት የማብቃትና መመሪያዎች የማዘጋጀት ሥራ ይሰራል። ምዝገባውን ለመጀመር የሚያስችሉ አጠቃላይ የዝግጅት ሥራ እንሰራለን።

አዲስ ዘመን፦ ኤጀንሲው አዲስ እንደመሆኑ መጠን በፌዴራልና በክልል በሰው ኃይልና በቁሳቁስ በሚፈለገው ደረጃ እያሟላ ነው?

ወይዘሮ ነፃነት፦በፌዴራል ደረጃ ዋነኛ የሥራ ዘርፎች የመረጃ ቅበላ፣ የወሳኝ ኩነቶች ጥናትና ምርምር የአሠራር ግንባታ፣ የትምህርትና ስልጠናና የቴክኖሎጂ የሥራ ሂደቶች ከሃምሳ በመቶ በላይ የሰው ኃይላቸውን አሟልተናል። በቀጣይም ሰባ አምስት በመቶ ለማድረስ እየሰራን ነው።

ሆኖም ዋና ችግር የሆነብን የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ለአገራችን አዲስ በመሆኑ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል የለም። ከተለያየ የሥራ መስክ የመጣውን ባለሙያ ማሰልጠን ትልቅ ፈተና ሆኖብናል። የኤጀንሲውን ባለሙያዎች ለማብቃት እየጣርን ነው። ቢሯችንን በቁሳቀስ ለማደራጀትም ተሞክሯል። ወደ ምዝገባው ስንገባ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያስፈልገናል። እስካሁን መንግሥት በጀት መድቦልናል። በቀጣይ የመንግሥት ብቻ በቂ ላይሆን ይችላል። ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር አብርን እንሰራለን።

ከአሁን በኋላ ትልቅ ሥራ የሚሆነው ክልሎች ጋር ያለው ነው። ብዙ ክልሎች ኤጀንሲያቸውን አቋቁመዋል። ነገር ግን ኤጀንሲያቸውን ማቋቋም ብቻ በቂ አይደለም። የወሳኝ ኩነቶች ትልቁ ሥራ የሚሰራው ቀበሌዎች ላይ ነው። በአገሪቱ ውስጥ ከአስራ ሰባት ሺ በላይ ቀበሌዎች አሉ። በየቀበሌው የሚከሰትን ኩነት ለመመዝገብ አደረጃጀቱ መመለስ አለበት። የሰው ኃይሉ ፍላጎት መለየት አለበት። ከቀበሌ ወደ ወረዳ፣ ወደ ዞን ከዚያም ወደ ክልልና ፌዴራል የሚኖረው ትስስር መፈታት አለበት። ሠራውን ለመጀመር ከፍተኛ ድርሻ ያላቸው ክልሎች ዝግጅታቸውን ካላጠናቀቁ መጀመር አስቸጋሪ ነው። አሁን ባለው ሁኔታ ጥሩ የሄዱ ክልሎች እንዳሉ ሁሉ ወደ ሥራም ያልገቡ አሉ። ስለዚህ ሁሉንም ወደ አንድ መስመር ማስገባት ትልቁ ፈተና ይሆናል።

አዲስ ዘመን ፦ክልሎችን በምን መልኩ ነው እያገዛችኋቸው ያላችሁት?

ወይዘሮ ነፃነት፦ለሁሉም ክልሎች የሚሰራ መመሪያ አዘጋጅተናል። በሁሉም ክልሎች ከቋንቋ በስተቀር ወጥ የሆነ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ እንዲኖር ነው የሚያስፈልገው። ወጥ የሆነ መረጃ ለመሰብሰብ በአገር ደረጃ የሁሉንም ባህል ያካተተ የአሠራር ሥርዓት ተቀርጿል። በሁለተኛ ደረጃ ከልሎችን ስልጠና በመስጠት ነው እያገዝን ያለነው። በዘን ድሮ ዓመት ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሠራ እንሰራለን ተብሎ ይጠበቃል። በቀበሌ ደረጃ ኩነቶችን የሚመ ዘግቡ አስራ ሰባት ሺ ሰዎችን እናሰ ለጥናለን። የተለያዩ አገሮች ልምድ ልውውጥ የማስቀ ስም ሥራ ይሰራል።

አዲስ ዘመን፦ ከቀበሌ እስከ ፌዴራል መረጃዎች ለመለዋወጥ የኢንፎርሜሽን ቴክኖ ሎጂን ትጠቀማላችሁ?

ወይዘሮ ነፃነት፦ ወደ ቴክኖሎጂ ከመሄዳችን በፊት የወረቀቱ ሥራ በተጣራ መልኩ መሠራት አለበት። ምክንያቱም የእጁ ሥራ ነው ወደ ቴክኖ ሎጂው የሚሸጋገረው። ለሁለት ዓመት ሥራ ላይ የምናውለው የእጅ ሥራ ነው። የእጁ ሥራ ያሰራናል የሚል እምነት ነው ያለው። በቀጣይ ግን በቴክኖሎጂ ለመታገዝ በጥናት ለመመለስ በእቅዳችን ይዘነዋል።

አዲስ ዘመን፦አዋጁ በ2007 ዓ.ም ምዝገባ እንደሚጀመር ነው ያስቀመጠው። ለምን አልጀመ ራችሁም?

ወይዘሮ ነፃነት፦አዋጁ እንደሚያስቀምጠው ሁለት ዓመት የዝግጅት ጊዜ ያስፈልጋል። እኛ ወደ ሥራ የገባነው አዋጁ ከወጣ ከአንድ ዓመት በኋላ ነው። አዋጁ እንደዋጣ ወዲያው ኤጀንሲው መቋቋም ነበረበት። ነገር ግን አልተቋቋመም። መተዳደሪያ ደንብ ወጥቶለት ወደ ሥራ የገባው በ2006 ዓ.ም ነው። አዋጁ ያስቀመጠው የዝግጅት ጊዜ አልተሰጠንም። ዘንድሮ የኩነቶች ምዝገባ ያልተጀመረው አንድ ዓመት ዘግይቶ በመቋቋሙ ነው። ዘግይቷል መባል ካለበት በትክክል የተሰጠውን የዝግጅት ጊዜ ተጠቅሞ ጨርሷል ወይም አልጨረሰም የሚል ከሆነ በተሰጠው ጊዜ መሠረት እየሰራ ነው። እንዲያም ሆኖ በአዋጁ ከተሰጠው ጊዜ በአንድ ዓመት ለመጨረስ ሰፊ ሥራ ተሰርቶ ነበር። ነገር ግን የኤጀንሲው ሥራ ብቻ በአገር ደረጃ የወሳኝ ኩነቶችን ለመመዝገብ በቂ አይደለም። ክልሎች መዘጋጀት ነበረባቸው። ክልሎች ኤጀን ሲያቸውን ቢያቋቁሙም ለመመዝገብ አልደረሱም። በዚህ ምክንያት ነው ዘንድሮ ምዝገባ ያልጀመረው።

አዲስ ዘመን፦ የፍትህ ሚኒስቴር፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ሌሎች የሚደግፏችሁ አካላት በምን ደረጃ እየደገፏችሁ ነው?

ወይዘሮ ነፃነት፦ተጠሪነታችን ለፍትህ ሚኒስቴር ነው። ፍትህ ሚኒስቴር የተቻለውን ያህል ለመደገፍ ጥረት እያደረገ ነው። ከኤጀንሲው ጋር በጋራ ገምግመን ችግሮች የሚፈቱበትን መፍትሔ እናስቀምጣለን። መደገፍ ባለበት እየደገፉን ነው። ፍትህ ሚኒስቴር የራሱ አንገብጋቢ ሥራ ስላለበት አሁን ከሚደግፈው በላይ መደገፍ አለበት ለማለት ትንሽ ያስቸግራል። የክልል ኤጀንሲዎችን ለመደገፍ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች የሥራው ባለቤቶች መሆን ይጠበቅባቸዋል። ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው። በአጠቃላይ ግን መደገፍ በሚገባው መጠን እየተደገፈ ነው ማለት አይቻልም። አዲስ ኤጀንሲ ለማቋቋም ትልቅ ፈተና አለው።

አዲስ ዘመን፦የኤጀንሲው ቦርድ ወቅቱን ጠብቆ አላካሄደም ምክንያቱ ምንድን ነው?

ወይዘሮ ነፃነት፦ቦርዱ በየወሩ እየተገናኘ የኤጀንሲውን ሥራ መገምገም እንዳለበት መመሪያ ደንቡ ያስቀምጣል። በየወሩ መካሄድ ነበረበት ግን አልተካሄደም። ያልተካሄደበት ምክንያት ሁለት ነው። የሚቀርቡ ውሳኔዎችን በየወሩ ቦርዱ ይዞ መቅረብን ችላ ብሎ ነበር። በሌላ በኩል ደግሞ ወቅቱን ጠብቆ የቦርድ አባላት በስብሰባ ላይ መገኘት አልቻሉም። ይህ ትክክል አለመሆኑ አዳማ ባካሄድነው ስብሰባ አንስተን ተነጋግረናል። ለማስተካከልም ተስማ ምተናል።

አዲስ ዘመን፦የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ በእርግጠኛነት መቼ ትጀምራላችሁ?

ወይዘሮ ነፃነት፦ በ2008 ዓ.ም መስከረም ወይም ጥቅምት ወር ላይ እንጀምራለን። ከቻልን ከዚያ በፊት ልንጅምር እንችላለን።

አዲስ ዘመን፦አብረዋችሁ የሚሰሩ አካላት ምዝገባውን ለማገዝ ምን ማድረግ አለባቸው ይላሉ?

ወይዘሮ ነፃነት፦ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ድርሻ ያላቸው አካላት እንደ ጤና ጥበቃ፣ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ፣ የፍትህ አካላት፣ ትምህርት ሚኒስቴርና ሌሎች ተቋማት ባለድርሻ አካላት በአዋጁ የተሰጠውን ኃላፊነቱን ለመወጣት በቂ ዝግጅት ማድረግ አለባቸው። እነኝህ አካላት በቂ ዝግጅት ካላደረጉ ምዝገባውን ለማካሄድ ተጽዕኖው ቀላል አይሆንም።

 

ከኤጀንሲው የሚገኘውን መረጃ የሚያወጣው ማዕካለዊ ስታትስቲክስ ስለሆነ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ራሱን መፈተሽና ዝግጅት ማድረግ አለበት። የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ የኤጀንሲው ሥራ ብቻ ሳይሆን የብዙ አካላት ትብብር ውጤት ነው። በመሆኑም በቂ ዝግጅት ማድረግ ይገባቸዋል። የኅብረተሰቡ ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው በኩነቶች መረጃ ላይ ተመስርቶ ነው። ስለሆነም ንቁ ተሳትፎ ማድረግ አለበት። የራሱ ጉዳይ ነው ብሎም ሊደግፈን ይገባል። ሚዲያዎችም ሥራዎቻችንን ለሕዝብ ጆሮ በማድረስ ሊተባበሩን ይገባል።


Editors Pick

Criminal Law Blog
የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 19 (6) ስለተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት እንዳላቸው ሆኖም በህግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ እንደሚችል በግልፅ ተመልክቷል፡፡ ከዚህ ህገ-መን...
904 hits
Comparative Law Blog
A free market economic system has been taken as a paradigm exposition for organizing and streamlining the relationship between state, private property owners and the community. Taking markets as a pan...
8300 hits
Contract Laws Blog
Does the law of sales applicable to contract for supply of software? Assume a government authority has bought a software from a software company. A defect in the software led to massive loss of money....
13739 hits
Arbitration Blog
Parties’ freedom to agree on any matter extends to agree to resolve their dispute either judicial litigation or arbitration. Arbitration is a system of dispute settlement where by disputants takes the...
11137 hits

Top Blog Posts

Labor and Employment Blog
  ዓለማችን ላይ የፈረንጆቹ 2020 የተወሳሰቡ ችግሮችን ይዞባት መጥቷል፡፡ ከቻይና ውሃን በትንሹ ተነስቶ በወራት ውስጥ ዓለምን ካዳረሰው የኮሮና ቫይረስ የሚስተካከል ችግር ግን ይመጣል ብሎ የገመተ አልነበረም፡፡ ይህ ቫይረስ በቀጥታ በሰው ልጆች ጤና እና ህይዎት ላይ እያሰከተለ ከሚገኘው ኪሳራ እና ውድመት በሚስተካከ...
Taxation Blog
  በዚህ ጽሑፍ ስለ ግብር ስወራ ምንነት፣ በተለያዩ የግብር ዓይነቶች ሥር የግብር ስወራ ስለሚያቋቋሙ ድርጊቶች፣ ለግብር ስወራ መነሻ ሊሆኑ ስለሚችሉ ምክንያቶች እንዲሁም የመከላከያ መንገዶቹ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡ ይህንን ጽሑፍ ለመጻፍ መነሻ የሆነኝ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጉምሩክና ታክስ ወንጀል ችሎት...
About the Law Blog
  መግቢያ የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ቀደም ሲል አውጥቶት የነበረውና የተከራየን ሰው ማስወጣት (በርግጥ ደንቡ ይህን ድርጊት አልከለከለም) እና የኪራይ ዋጋን መጨመር ለማገድ የወጣውን የደንብ ቁጥር 122/13 ማራዘሙን በድጋሜ አስታዉቋል፡፡ ይህ ደንብ የቤት አከራዮች ያከራዬት ቤት ላይ ዋጋ እንዳንይጨምሩ ...
Taxation Blog
It is perplexing for me, as a tax lawyer having worked for close to 10 years on Ethiopian tax laws, to see how the investment and finance community in Ethiopia is not worrying enough about the tax on ...